Blog1 Both Sidebar

11
Mar 2023

በፊንላንድ ዩቫስኲላ ኹተማ ዚቅዱስ ዑራኀል ጜዋዕ ማኅበር ተመሠሚተ። በኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት አጥቢያ ቀተ ክርስቲያን እዚተገለገሉ ዹሚገኙ በዩቫስኲላ ኹተማ ዚሚኖሩ ምእመናን መጋቢት ፪/፳፻፲፭ ዓ.ም በቅዱስ ዑራኀል ስም ዚጜዋዕ ማኅበር መሠሚቱ። በዝርወቱ ዓለም ዚሚኖሩ ምእመናን በዚወሩ እዚተሰበሰቡ በጋራ በአንድነት በቅዱሳን ስም ዚጜዋዕ ማኅበር መሥርተው ይጞልያሉ ፣ይማጞናሉ አመቺ በሆነ ጊዜም ቅዳሎ ይቀደስላ቞ዋል ፣ በዚሁ መሠሚት በፊንላንድ ዩቫስኲላ ኹተማ ዹሚገኙ ምእመናን እጣ በመጣል በተደጋጋሚ ቅዱስ ዑራኀል በመውጣቱ በመልአኩ ቅዱስ ዑራኀል ስም ዚጜዋዕ ማኅበር ተመሥርቷል ። በዕለቱ ዚሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቀተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአኹ አሚን ቀሲስ ለማ......

Read More


02
Feb 2023

ጥር 23 ቀን 2015 ዓ.ም፥ በስዊድን፣ ስካንዲናቪያንና ዚግሪክ ሀገሮቜ ሀገሹ ስብኚት በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቀተ ክርስቲያን ለጜጌ ሃይማኖት ስንበት ትምህርት ቀት ተተኪ መዘምራን ‹‹ ብላ቎ናነትን ዚመቀደስ ጥበብ በቀተ ክርስቲያን ›› በሚል ርእስ በመምህር ታደሰ ወርቁ ሥልጠና ተስጥቷል። ሥልጠናውን ዚወሰዶት አብዛኛዎቹ ብላ቎ናዎቜ በፊንላንድ ተወልደው ዹአደጉ ናቾው ። በዚህም ዚሥልጠና ርእሰ ጉዳይ ዚብላ቎ናነትና ብላ቎ናነትን ዚመቀደስ ምንነት፣ ብላ቎ናነትን ዚመቀደስ ጥበብ ምን ምን እንደሆነ ተዳስሷል። ዚደብሩም ተተኪ መዘምራን ልዩ ልዩ ጥያቄዎቜን አንስተውፀ ለተነሱት ጥያቄዎቜ በአሥልጣኙና በደብሩ አስተዳዳሪ ሰፊ ማብራሪያይና መልስ ተስጥቷል።...

Read More


27
Jan 2023

On January 24, 2023, in the Diocese of Sweden, Scandinavia and Greek countries, in Helsinki, Finland, Debre Amin Abune Teklehaymont Church, a mandate was held that took into account the cognitive challenge faced by our Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. In the training program under the title of “The Sustainability of Spiritual Servants in Times of Crisis”, the General Manager of the Diocese of Sweden, Scandinavia and Greek Countries and the Administrator of Debre Amin Abune Teklehaymont Church of Helsinki, Finland; d.n. Tadesse Worku has given physical and online training to parish council......

Read More


25
Jan 2023

ጥር 16 ቀን 2015 ዓ.ም፥ በስዊድን፣ ስካንዲናቪያንና ዚግሪክ ሀገሮቜ ሀገሹ ስብኚት በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቀተ ክርስቲያን ፥ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያናቜን ዚገጠማትን ውቅታዊ ፈተና ታሳቢ ያደሚገ ሥልጣን ተካሂዷል። በሥልጠናው መርሐ ግብር ‹‹ ዚመንፊሳዊ አገልጋዮቜ ሡታፌ በዘመነ ቀውስ ›› በሚል ርእስ÷በስዊድን፣ ስካንዲናቪያንና ዚግሪክ ሀገሮቜ ሀገሹ ስብኚት ዋና ሥራ አስኪያጅና ዚፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቀተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ሰብሳቢነትፀ በመምህር ታደሰ ወርቁ ለሰበካ ጉባኀ አባላት፣ ለልዩ ልዩ ክፍል ሐላፊዎቜና ለንዑስ ክፍል ተጠሪዎቜ በአካልና በበዹነ መሚብ ሥልጠና ተሰጥቷል። በዚህም ሥልጠና ዚመንፈሳዊ አገልጋዮቜ ለአገልግሎት ዚመታጚት ሂደቶቜ፣ በአሁን ጊዜ ቀተ ክርስቲያን ዚገጠማት......

Read More


22
Jan 2023

ዚስዊድን፣ ስካንዲናቪያንና ዚግሪክ ሀገሮቜ ሀገሹ ስብኚት በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቀተ ክርስቲያን፣ ጥር 13 ቀን 2015 ዓ.ም ዚጌታቜን ዚመድኃኒታቜን ዚኢዚሰሱ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በርካታ ምእመናን በተገኘበት በድምቀት ተኚብሯል። ዹበዓሉ ሥነ ሥርዓት ዚስዊድን፣ ስካንዲናቪያንና ዚግሪክ ሀገሮቜ ሀገሹ ስብኚት ዋና ሥራ አስኪያጅና ዚደብሚ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቀተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ በሆኑት በመልአኹ አሚን ዚተመራ ሲሆንፀ በዓሉን ዹተመለኹ ትምህርት ኚኢትዮጵያ በመጡት በዲያቆን ታደሰ ወርቁ ትምህርት ተሰጥቷል። በፊንላንድ ተወልደው ያደጉ ዚሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ዚጜጌ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቀት ተማሪዎቜ ተተኪ መዘምራንም በዓሉን ዚሚያዘክሚውን ያሬዳዊ መዝሙር አቅርበዋል።...

Read More


01
Nov 2022

በመ/ር አቀል አሰፋ (ኢኊተቀ ቎ቪ ጥቅምት ፳፪ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም አዲስ አበባ) በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ፣ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጚጌ ዘመንበሹ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት መሪነት ዚቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በመንበሹ ፓትርያርክ ቅብዓ ሜሮን ዚማፍላት ዚጞሎት መርሐ ግብር እዚተካሄደ ይገኛል። ቀድሞ ኚግብፅ ተዘጋጅቶ ይመጣ ዹነበሹው ቅብዓ ሜሮን በኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ሲዘጋጅ ይህ ለ፫ ተኛ ጊዜ ነው። ማለዳ ጠዋት ፲ ሰዓት በተጀመሹው ሥርዓተ ቀተክርስቲያን ; ምእመናንና ካህናት ለ፯ ተኚታታይ ቀናት በጞሎት እንዲተባበሩ ቀደም ብሎ በቅዱስነታ቞ው ጥሪ ቀርቧል። ይህንኑ አስመልክቶ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ......

Read More


29
Sep 2022
ዚ፳፻፲፭ ዓ.ም መስቀል ደመራ በዓል በሄልሲንኪ ፊንላንድ በደማቅ ሥነሥርዓት ተኹበሹ

በኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ዚሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት እና በኀርትራ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ዚሄልሲንኪ ሐመሚ ኖኅ ቅድስት ማርያም አቢያተ ክርስቲያን በአንድነት ዚመስቀልን ደመራ በዓል በደማቅ ሥነ ሥርዓት አኚበሩ። በዕለቱ ኢትዮጵያውያን እና ኀርትራውያን ካህናት እና ምእመናን ኹመላዋ ፊንላንድ ዚመጡ በአንድነት በቊታው ተገኝተዋል።በተጚማሪም በክብር እንግድነትም ዚሂልሲንኪ ኊርቶዶክስ ቀተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሊዮ ዋና ፀሐፊ ቀሲስ ላዛርዩስ ተገኝተው ለሕዝበ ክርስቲያኑ መልእክት አስተላልፈዋል።   በመጚሚሻም ዚሁለቱ አድባራት አስተዳዳሪዎቜ ፣መልአኚ አሚን ቀሲስ ለማ በሱፍቃድና ሊቀ ብርሃናት ቀሲስ አንገሶም ዕቁባይ ትምህርት ኚሰጡ በኋላ ደመራው ተለኩሶ ሕዝበ ክርስቲያኑ በጋራ ዝማሬ ዘምሹው ዹበዓሉ ፍጻሜ ሆኖአል።...

Read More


21
Aug 2022
ዚደብሚ ታቊር በዓል በሄልሲንኪ በደማቅ ሥነ ሥርዓት ተኹበሹ

በሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቀተ ክርስቲያን ዚደብሚ ታቊር በዓል ዚደብሩ ሕጻናት አዳጊ ልጆቜ በተገኙበት በደማቅ ሥነ ሥርዓት ተኚብሯል ። ዚሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለሃይሜኖት ቀተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአኹ አሚን ቀሲስ ለማ በሱፍቃድ በበዓሉ ላይ እንደተናገሩት በተለይ በዝርወቱ ዓለም ተወልደው ዚሚያድጉ ተተኪው ትውልድ ዚበዓላትን አኚባበር እንዲሁም ትውፊታዊውንም ቅብብል በተግባር ያውቁ ዘንድ እንዲያስቜል ታስቊ ዹተዘጋጀ ነው ብለዋል። ወላጆቜም ለዚሁ ትልቅ አስተዋጜዖ ያደርጋሉ ብለዋል ። በቀጣይ ዚኢትዮጵያ ዘመን መለወጫ አዲስ ዓመትም እንዲሁ በደሜቅ ሥነ ሥርዓት እንደሚኚበር ጠቁመዋል። በተያያዘ ዜና ነሐሮ 14 /2014 ዓ.ም በታምፔሬ ኹተማ በታምፔሬ ዹሚገኙ ዚቅድስት ኪዳነ ምሕሚት ጜዋዕ ማኅበር አባላት......

Read More


25
Jul 2021
ዚአገልግሎት ምስጋና መርሐ ግብር ተዘጋጀ

በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቀተ ክርስቲያን ለወ/ሮ አለማቜ ገብሚ ሚካኀል ዚአገልግሎት ዚምስጋና ምስክር ወሚቀት ተሰጠ። በሀገሹ ፊንላንድ ኚሊስት ዐሥርት ዓመታት በላይ በመንፈሳዊ አገልግሎት በማኅበራዊ አገልግሎት ለሚታውቁት ወ/ሮ አለማቜ ፣ ሐምሌ ፲፯/፳፻፲፫ ዓ.ም በሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቀተ ክርስቲያን ዚአገልግሎት ዚምስጋና መርሐ ግብር ተዘጋጀ ። በዕለቱም በመርሐግብሩ ዚታደሙት ምእመናን ወ/ሮ አለማቜ በሀገሹ ፊንላንድ በስደት ለሚገኙት ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያ ያዘነውን በማጜናናት ፣ በመጠዹቅ ዹሀገሹ ፊንላንድንም ሥርዓተ ሀገሩንም በማለማመድ ኹፍተኛ አገልግሎት ማበርኚታ቞ውን ተናግሹዋል ። ወ/ሮ አለማቜ በተለይ በመንፈሳዊ ሕይወታ቞ው ኚታላቁ ካህን አባታ቞ውና ኚለጋሷ እናታ቞ው ዚወሚሱትን በጎ ተግባር ስደቱ ተጜእኖ ሳይፈጥርባ቞ው ሃይማኖታዊ ሥርዓታ቞ውን......

Read More


26
Dec 2020

በኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን በስዊድንና ስካንድኔቪያን ሀገሮቜ ሀገሹ ስብኚት በፊንላንድ ዚሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለ ቀተክርስቲያን እሑድ ታኅሣሥ 11 ቀን /2013 (20.12.2020) በርቀት በስካይፔ ባካሄደው ዓመታዊ ዚአጥቢያ ምእመናን መንፈሳዊ ጠቅላላ ጉባኀ ላይ በፈሚንጆቹ ኹ2021 ዓ.ም ጀምሮ በደብሩ ዚውስጥ መተዳደሪያ ደንብ መሠሚት ለቀጣይ ሁለት ዓመታት ቀተክርስቲያኗን ዚሚያገለግሉ አዲስ ዚሰበካ መንፈሳዊ ጉባኀ አባላ ምርጫን አካሄዷል። ጠቅላላ ጉባኀውን በጞሎት ክፍተው ዚመሩት ዚደብሩ አስተዳዳሪ መልአኹ አሚን ቀሲስ ለማ በሱፍቃድ ዚዕለቱን አጀንዳዎቜ ማለትም  ዚደብሩን ዚውስጥ መተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ ነጥቊቜ ላይ ተወያይቶ ማጜደቅ  ዹ2021 በጀት ዓመት ማጜደቅ  ዚሰበካ ጉባኀ ምርጫ ማኹናወን መሆናቾውን ገልጠዋል ። ዹጠቅላላ ጉባኀ ዚምርጫው......

Read More


Social Icons

Calendar

March 2023
M T W T F S S
 12345
6789101112
13141516171819
20212223242526
2728293031  

instagram

    flickr

    instagram