Uncategorized


04
Oct 2023

ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን  ለማኅሌት አገልግሎት ኚምትጠቀምባ቞ው መጻሕፍት መካኚል አንዱ ዹሆነው ዹማኅሌተ ጜጌ መጜሐፍ ወደ ፊንላንድኛ ቋንቋ ተተርጎመ። ይህንን ዚአባ ጜጌ ድንግል ድርሰት ዹሆነው መጜሐፍ ዚተሚጎሙት ዚፊንላንድ ሀገር ዜጋ  ዚሆኑት እና ኚሃምሳ ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ለአምስት ዓመታት ቆይታ ያደሚጉት አቶ ኒሎ ሆንካነን ና቞ው። ተርጓሚው መጜሐፉ ወደ ፊንላንድኛ ለመተርጎም ኹ10 ዓመት በላይ ሲያጠኑ እንደቆዩና ዋና ምንጭ አድርገው ዚተጠቀሙት ደግሞ በ1919 ዓ.ም. በዶ/ር አዶልፍ ግሮህማን ዹተተሹጎመውን ዹጀርመንኛ ቅጅ እንደሆነ ገልጞዋል። አቶ ኒሎ ማኅሌተ ጜጌን ለምን ለመተርጎም እንዳነሳሳ቞ው ሲጠዚቁፀ «ማኅሌተ ጜጌ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ካሏት ዹመዝሙር መጻሕፍት ውስጥ በትንሜ ጥራዝ መጜሐፍ ሆኖ......

Read More


03
Sep 2023
ሀገሹ ስብኚቱ ዹ2015 በጀት ዓመት  አፈጻጞም ጠቅላላ ጉባኀውን  አጠናቀቀ

ዜና ሀገሹ ስብኚት: ዚስዊድን፣ስካንዲናቪያን እና ግሪክ ሀገሮቜ  ሀገሹ ስብኚት ፣ ኹነሐሮ 26-27/2015 ዓ.ም በስዊድን ስቶክሆልም ሲያካሂድ ዹነበሹውን ዹሀገሹ ስብኚቱን ዹ2015 በጀት ዓመት  አፈጻጞም ጠቅላላ ጉባኀውን  አጠናቀቀ። በብፁዕ አቡነ ኀልያስ ዚሚመራው ዚስዊድን፣ስካንዲናቪያን እና ግሪክ ሀገሮቜ ሀገሹ ስብኚት በጉባኀው ላይ ዹ2015 ዓ.ም ዚበጀት ዓም ዚሥራ አፈጻጞም ዹገመገመ ሲሆን  ያጋጠሙ ቜግሮቜን በማንሳት ውይይት አድርጓል ።በማያያዝም ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ዚሚያገለግል ስልታዊ ዕቅድ ቀርቩ ውይይት ዚተደሚገበት ሲሆን ቀደም ብሎ በአገልግሎት ላይ ያለውን ዹሀገሹ ስብኚቱን መተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ ሹቂቅ ሕግም  ለጉባኀው ቀርቩ ውይይት ተደርጎበታል ። በመጚሚሻም ጉባኀው በወቅታዊ ዚቀተ ክርስቲያናቜን ፈተናዎቜ እና በሀገራቜን ኢትዮጵያ እስካሁን ሊቆም ያልቻለው ዚእርስ......

Read More


03
Sep 2023

ነሐሮ 24 ቀን 2015 +++ ብፁዕ አቡነ ኀልያስ ዚስዊድን፣ ስካንድንቪያን እና ግሪክ ሀገሮቜ ሊቀ ጳጳስ በሀገሹ ፊንላንድ ዋና ኹተማ ዚሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ሕንጻ ቀተ ክርስቲያን ነሐሮ 18 ቀን 2015 ዓ.ም ባርኚዋል። ዚሄልሊንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቀተክርስቲያን በ2004 ዓ.ም በብፁዕ አቡነ እንጊንስ ተባርኮ አገልግሎቱን ዹጀመሹው እንደሆነ ያገኘነው መሹጃ ያመለክታል። አጥቢያው እስኚ አሁን ድሚስ ኚፊንላንድ ኊርቶዶክስ ቀተ ክርስቲያን በውሰት በሚያገኘው ሕንጻ ቀተ ክርስቲያን ላይ በወር ሁለት ጊዜ እና በዐበይት በላይ ጊዜ ብቻ አገልግሎት እዚሰጠ መቆዚቱን ተገልጿል። በአሁን ጊዜ ዚሕጻናት እና አዳጊ ልጆቜ እንዲሁም ዹምዕመንናን ቁጥር እዚተበራኚተ በመምጣቱ ዚተነሳፀ በዚዕለቱ ምዕመናን እግዚአብሔርን......

Read More


03
Sep 2023
Archbishop Consecrates New Church Building in Helsinki, Finland

+++ Helsinki, Finland – August 27, 2023 In a momentous ceremony, His Grace Abune Elias, the Archbishop of Sweden, Scandinavia, and Greece, presided over the consecration of the brand-new Church building for the DebreAmin Abune Teklehaymanot Church in the heart of Helsinki, Finland. The consecration took place on August 26, 2023, marking a significant milestone for the local Christian community. The Helsinki DebreAmin Abune Teklehaymanot Church, originally blessed by His Grace Abune Antonis, commenced its service back in 2011. However, until recently, the parish had been conducting spiritual services only twice a......

Read More


11
Mar 2023

በፊንላንድ ዩቫስኲላ ኹተማ ዚቅዱስ ዑራኀል ጜዋዕ ማኅበር ተመሠሚተ። በኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት አጥቢያ ቀተ ክርስቲያን እዚተገለገሉ ዹሚገኙ በዩቫስኲላ ኹተማ ዚሚኖሩ ምእመናን መጋቢት ፪/፳፻፲፭ ዓ.ም በቅዱስ ዑራኀል ስም ዚጜዋዕ ማኅበር መሠሚቱ። በዝርወቱ ዓለም ዚሚኖሩ ምእመናን በዚወሩ እዚተሰበሰቡ በጋራ በአንድነት በቅዱሳን ስም ዚጜዋዕ ማኅበር መሥርተው ይጞልያሉ ፣ይማጞናሉ አመቺ በሆነ ጊዜም ቅዳሎ ይቀደስላ቞ዋል ፣ በዚሁ መሠሚት በፊንላንድ ዩቫስኲላ ኹተማ ዹሚገኙ ምእመናን እጣ በመጣል በተደጋጋሚ ቅዱስ ዑራኀል በመውጣቱ በመልአኩ ቅዱስ ዑራኀል ስም ዚጜዋዕ ማኅበር ተመሥርቷል ። በዕለቱ ዚሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቀተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአኹ አሚን ቀሲስ ለማ......

Read More


02
Feb 2023

ጥር 23 ቀን 2015 ዓ.ም፥ በስዊድን፣ ስካንዲናቪያንና ዚግሪክ ሀገሮቜ ሀገሹ ስብኚት በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቀተ ክርስቲያን ለጜጌ ሃይማኖት ስንበት ትምህርት ቀት ተተኪ መዘምራን ‹‹ ብላ቎ናነትን ዚመቀደስ ጥበብ በቀተ ክርስቲያን ›› በሚል ርእስ በመምህር ታደሰ ወርቁ ሥልጠና ተስጥቷል። ሥልጠናውን ዚወሰዶት አብዛኛዎቹ ብላ቎ናዎቜ በፊንላንድ ተወልደው ዹአደጉ ናቾው ። በዚህም ዚሥልጠና ርእሰ ጉዳይ ዚብላ቎ናነትና ብላ቎ናነትን ዚመቀደስ ምንነት፣ ብላ቎ናነትን ዚመቀደስ ጥበብ ምን ምን እንደሆነ ተዳስሷል። ዚደብሩም ተተኪ መዘምራን ልዩ ልዩ ጥያቄዎቜን አንስተውፀ ለተነሱት ጥያቄዎቜ በአሥልጣኙና በደብሩ አስተዳዳሪ ሰፊ ማብራሪያይና መልስ ተስጥቷል።...

Read More


27
Jan 2023

On January 24, 2023, in the Diocese of Sweden, Scandinavia and Greek countries, in Helsinki, Finland, Debre Amin Abune Teklehaymont Church, a mandate was held that took into account the cognitive challenge faced by our Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. In the training program under the title of “The Sustainability of Spiritual Servants in Times of Crisis”, the General Manager of the Diocese of Sweden, Scandinavia and Greek Countries and the Administrator of Debre Amin Abune Teklehaymont Church of Helsinki, Finland; d.n. Tadesse Worku has given physical and online training to parish council......

Read More


25
Jan 2023

ጥር 16 ቀን 2015 ዓ.ም፥ በስዊድን፣ ስካንዲናቪያንና ዚግሪክ ሀገሮቜ ሀገሹ ስብኚት በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቀተ ክርስቲያን ፥ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያናቜን ዚገጠማትን ውቅታዊ ፈተና ታሳቢ ያደሚገ ሥልጣን ተካሂዷል። በሥልጠናው መርሐ ግብር ‹‹ ዚመንፊሳዊ አገልጋዮቜ ሡታፌ በዘመነ ቀውስ ›› በሚል ርእስ÷በስዊድን፣ ስካንዲናቪያንና ዚግሪክ ሀገሮቜ ሀገሹ ስብኚት ዋና ሥራ አስኪያጅና ዚፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቀተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ሰብሳቢነትፀ በመምህር ታደሰ ወርቁ ለሰበካ ጉባኀ አባላት፣ ለልዩ ልዩ ክፍል ሐላፊዎቜና ለንዑስ ክፍል ተጠሪዎቜ በአካልና በበዹነ መሚብ ሥልጠና ተሰጥቷል። በዚህም ሥልጠና ዚመንፈሳዊ አገልጋዮቜ ለአገልግሎት ዚመታጚት ሂደቶቜ፣ በአሁን ጊዜ ቀተ ክርስቲያን ዚገጠማት......

Read More


22
Jan 2023

ዚስዊድን፣ ስካንዲናቪያንና ዚግሪክ ሀገሮቜ ሀገሹ ስብኚት በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቀተ ክርስቲያን፣ ጥር 13 ቀን 2015 ዓ.ም ዚጌታቜን ዚመድኃኒታቜን ዚኢዚሰሱ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በርካታ ምእመናን በተገኘበት በድምቀት ተኚብሯል። ዹበዓሉ ሥነ ሥርዓት ዚስዊድን፣ ስካንዲናቪያንና ዚግሪክ ሀገሮቜ ሀገሹ ስብኚት ዋና ሥራ አስኪያጅና ዚደብሚ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቀተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ በሆኑት በመልአኹ አሚን ዚተመራ ሲሆንፀ በዓሉን ዹተመለኹ ትምህርት ኚኢትዮጵያ በመጡት በዲያቆን ታደሰ ወርቁ ትምህርት ተሰጥቷል። በፊንላንድ ተወልደው ያደጉ ዚሄልሲንኪ ደብሚ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ዚጜጌ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቀት ተማሪዎቜ ተተኪ መዘምራንም በዓሉን ዚሚያዘክሚውን ያሬዳዊ መዝሙር አቅርበዋል።...

Read More


01
Nov 2022

በመ/ር አቀል አሰፋ (ኢኊተቀ ቎ቪ ጥቅምት ፳፪ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም አዲስ አበባ) በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ፣ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጚጌ ዘመንበሹ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት መሪነት ዚቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በመንበሹ ፓትርያርክ ቅብዓ ሜሮን ዚማፍላት ዚጞሎት መርሐ ግብር እዚተካሄደ ይገኛል። ቀድሞ ኚግብፅ ተዘጋጅቶ ይመጣ ዹነበሹው ቅብዓ ሜሮን በኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ሲዘጋጅ ይህ ለ፫ ተኛ ጊዜ ነው። ማለዳ ጠዋት ፲ ሰዓት በተጀመሹው ሥርዓተ ቀተክርስቲያን ; ምእመናንና ካህናት ለ፯ ተኚታታይ ቀናት በጞሎት እንዲተባበሩ ቀደም ብሎ በቅዱስነታ቞ው ጥሪ ቀርቧል። ይህንኑ አስመልክቶ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ......

Read More