Uncategorized


04
Oct 2023

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  ለማኅሌት አገልግሎት ከምትጠቀምባቸው መጻሕፍት መካከል አንዱ የሆነው የማኅሌተ ጽጌ መጽሐፍ ወደ ፊንላንድኛ ቋንቋ ተተርጎመ። ይህንን የአባ ጽጌ ድንግል ድርሰት የሆነው መጽሐፍ የተረጎሙት የፊንላንድ ሀገር ዜጋ  የሆኑት እና ከሃምሳ ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ለአምስት ዓመታት ቆይታ ያደረጉት አቶ ኒሎ ሆንካነን ናቸው። ተርጓሚው መጽሐፉ ወደ ፊንላንድኛ ለመተርጎም ከ10 ዓመት በላይ ሲያጠኑ እንደቆዩና ዋና ምንጭ አድርገው የተጠቀሙት ደግሞ በ1919 ዓ.ም. በዶ/ር አዶልፍ ግሮህማን የተተረጎመውን የጀርመንኛ ቅጅ እንደሆነ ገልጸዋል። አቶ ኒሎ ማኅሌተ ጽጌን ለምን ለመተርጎም እንዳነሳሳቸው ሲጠየቁ፤ «ማኅሌተ ጽጌ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካሏት የመዝሙር መጻሕፍት ውስጥ በትንሽ ጥራዝ መጽሐፍ ሆኖ......

Read More


03
Sep 2023
ሀገረ ስብከቱ የ2015 በጀት ዓመት  አፈጻጸም ጠቅላላ ጉባኤውን  አጠናቀቀ

ዜና ሀገረ ስብከት: የስዊድን፣ስካንዲናቪያን እና ግሪክ ሀገሮች  ሀገረ ስብከት ፣ ከነሐሴ 26-27/2015 ዓ.ም በስዊድን ስቶክሆልም ሲያካሂድ የነበረውን የሀገረ ስብከቱን የ2015 በጀት ዓመት  አፈጻጸም ጠቅላላ ጉባኤውን  አጠናቀቀ። በብፁዕ አቡነ ኤልያስ የሚመራው የስዊድን፣ስካንዲናቪያን እና ግሪክ ሀገሮች ሀገረ ስብከት በጉባኤው ላይ የ2015 ዓ.ም የበጀት ዓም የሥራ አፈጻጸም የገመገመ ሲሆን  ያጋጠሙ ችግሮችን በማንሳት ውይይት አድርጓል ።በማያያዝም ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚያገለግል ስልታዊ ዕቅድ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን ቀደም ብሎ በአገልግሎት ላይ ያለውን የሀገረ ስብከቱን መተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ ረቂቅ ሕግም  ለጉባኤው ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል ። በመጨረሻም ጉባኤው በወቅታዊ የቤተ ክርስቲያናችን ፈተናዎች እና በሀገራችን ኢትዮጵያ እስካሁን ሊቆም ያልቻለው የእርስ......

Read More


03
Sep 2023

ነሐሴ 24 ቀን 2015 +++ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የስዊድን፣ ስካንድንቪያን እና ግሪክ ሀገሮች ሊቀ ጳጳስ በሀገረ ፊንላንድ ዋና ከተማ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ነሐሴ 18 ቀን 2015 ዓ.ም ባርከዋል። የሄልሊንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን በ2004 ዓ.ም በብፁዕ አቡነ እንጦንስ ተባርኮ አገልግሎቱን የጀመረው እንደሆነ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። አጥቢያው እስከ አሁን ድረስ ከፊንላንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በውሰት በሚያገኘው ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ላይ በወር ሁለት ጊዜ እና በዐበይት በላይ ጊዜ ብቻ አገልግሎት እየሰጠ መቆየቱን ተገልጿል። በአሁን ጊዜ የሕጻናት እና አዳጊ ልጆች እንዲሁም የምዕመንናን ቁጥር እየተበራከተ በመምጣቱ የተነሳ፤ በየዕለቱ ምዕመናን እግዚአብሔርን......

Read More


03
Sep 2023
Archbishop Consecrates New Church Building in Helsinki, Finland

+++ Helsinki, Finland – August 27, 2023 In a momentous ceremony, His Grace Abune Elias, the Archbishop of Sweden, Scandinavia, and Greece, presided over the consecration of the brand-new Church building for the DebreAmin Abune Teklehaymanot Church in the heart of Helsinki, Finland. The consecration took place on August 26, 2023, marking a significant milestone for the local Christian community. The Helsinki DebreAmin Abune Teklehaymanot Church, originally blessed by His Grace Abune Antonis, commenced its service back in 2011. However, until recently, the parish had been conducting spiritual services only twice a......

Read More


11
Mar 2023

በፊንላንድ ዩቫስኲላ ከተማ የቅዱስ ዑራኤል ጽዋዕ ማኅበር ተመሠረተ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን እየተገለገሉ የሚገኙ በዩቫስኲላ ከተማ የሚኖሩ ምእመናን መጋቢት ፪/፳፻፲፭ ዓ.ም በቅዱስ ዑራኤል ስም የጽዋዕ ማኅበር መሠረቱ። በዝርወቱ ዓለም የሚኖሩ ምእመናን በየወሩ እየተሰበሰቡ በጋራ በአንድነት በቅዱሳን ስም የጽዋዕ ማኅበር መሥርተው ይጸልያሉ ፣ይማጸናሉ አመቺ በሆነ ጊዜም ቅዳሴ ይቀደስላቸዋል ፣ በዚሁ መሠረት በፊንላንድ ዩቫስኲላ ከተማ የሚገኙ ምእመናን እጣ በመጣል በተደጋጋሚ ቅዱስ ዑራኤል በመውጣቱ በመልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ስም የጽዋዕ ማኅበር ተመሥርቷል ። በዕለቱ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ አሚን ቀሲስ ለማ......

Read More


02
Feb 2023

ጥር 23 ቀን 2015 ዓ.ም፥ በስዊድን፣ ስካንዲናቪያንና የግሪክ ሀገሮች ሀገረ ስብከት በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ለጽጌ ሃይማኖት ስንበት ትምህርት ቤት ተተኪ መዘምራን ‹‹ ብላቴናነትን የመቀደስ ጥበብ በቤተ ክርስቲያን ›› በሚል ርእስ በመምህር ታደሰ ወርቁ ሥልጠና ተስጥቷል። ሥልጠናውን የወሰዶት አብዛኛዎቹ ብላቴናዎች በፊንላንድ ተወልደው የአደጉ ናቸው ። በዚህም የሥልጠና ርእሰ ጉዳይ የብላቴናነትና ብላቴናነትን የመቀደስ ምንነት፣ ብላቴናነትን የመቀደስ ጥበብ ምን ምን እንደሆነ ተዳስሷል። የደብሩም ተተኪ መዘምራን ልዩ ልዩ ጥያቄዎችን አንስተው፤ ለተነሱት ጥያቄዎች በአሥልጣኙና በደብሩ አስተዳዳሪ ሰፊ ማብራሪያይና መልስ ተስጥቷል።...

Read More


27
Jan 2023

On January 24, 2023, in the Diocese of Sweden, Scandinavia and Greek countries, in Helsinki, Finland, Debre Amin Abune Teklehaymont Church, a mandate was held that took into account the cognitive challenge faced by our Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. In the training program under the title of “The Sustainability of Spiritual Servants in Times of Crisis”, the General Manager of the Diocese of Sweden, Scandinavia and Greek Countries and the Administrator of Debre Amin Abune Teklehaymont Church of Helsinki, Finland; d.n. Tadesse Worku has given physical and online training to parish council......

Read More


25
Jan 2023

ጥር 16 ቀን 2015 ዓ.ም፥ በስዊድን፣ ስካንዲናቪያንና የግሪክ ሀገሮች ሀገረ ስብከት በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ፥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን የገጠማትን ውቅታዊ ፈተና ታሳቢ ያደረገ ሥልጣን ተካሂዷል። በሥልጠናው መርሐ ግብር ‹‹ የመንፊሳዊ አገልጋዮች ሡታፌ በዘመነ ቀውስ ›› በሚል ርእስ÷በስዊድን፣ ስካንዲናቪያንና የግሪክ ሀገሮች ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅና የፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ሰብሳቢነት፤ በመምህር ታደሰ ወርቁ ለሰበካ ጉባኤ አባላት፣ ለልዩ ልዩ ክፍል ሐላፊዎችና ለንዑስ ክፍል ተጠሪዎች በአካልና በበየነ መረብ ሥልጠና ተሰጥቷል። በዚህም ሥልጠና የመንፈሳዊ አገልጋዮች ለአገልግሎት የመታጨት ሂደቶች፣ በአሁን ጊዜ ቤተ ክርስቲያን የገጠማት......

Read More


22
Jan 2023

የስዊድን፣ ስካንዲናቪያንና የግሪክ ሀገሮች ሀገረ ስብከት በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን፣ ጥር 13 ቀን 2015 ዓ.ም የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሰሱ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በርካታ ምእመናን በተገኘበት በድምቀት ተከብሯል። የበዓሉ ሥነ ሥርዓት የስዊድን፣ ስካንዲናቪያንና የግሪክ ሀገሮች ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅና የደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ በሆኑት በመልአከ አሚን የተመራ ሲሆን፤ በዓሉን የተመለከ ትምህርት ከኢትዮጵያ በመጡት በዲያቆን ታደሰ ወርቁ ትምህርት ተሰጥቷል። በፊንላንድ ተወልደው ያደጉ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት የጽጌ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች ተተኪ መዘምራንም በዓሉን የሚያዘክረውን ያሬዳዊ መዝሙር አቅርበዋል።...

Read More


01
Nov 2022

በመ/ር አቤል አሰፋ (ኢኦተቤ ቴቪ ጥቅምት ፳፪ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም አዲስ አበባ) በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ፣ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት መሪነት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በመንበረ ፓትርያርክ ቅብዓ ሜሮን የማፍላት የጸሎት መርሐ ግብር እየተካሄደ ይገኛል። ቀድሞ ከግብፅ ተዘጋጅቶ ይመጣ የነበረው ቅብዓ ሜሮን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሲዘጋጅ ይህ ለ፫ ተኛ ጊዜ ነው። ማለዳ ጠዋት ፲ ሰዓት በተጀመረው ሥርዓተ ቤተክርስቲያን ; ምእመናንና ካህናት ለ፯ ተከታታይ ቀናት በጸሎት እንዲተባበሩ ቀደም ብሎ በቅዱስነታቸው ጥሪ ቀርቧል። ይህንኑ አስመልክቶ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ......

Read More