የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በቫሳ ከተማ ተከበረ

የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በቫሳ ከተማ ተከበረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የቤተክርስቲያን ሰሜን ምዕራብ አውሮፖ ሀገረ ስብከት በፊንላንድ ቫሳ ከተማ የሚኖሩ ምእመናን ባቋቋሙት የቅዱስ ገብርኤል ጽዋዕ ማኅበር አስተባባሪነት ዓመታዊው የቅዱስ ገብርኤል በዓል ባሳለፍነው ቅዳሜ ታኅሣሥ 14 ቀን 2010 ዓ.ም በሥርዓተ ቅዳሴና በጉባኤ ተከብሮ ውሏል። በሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን የሚያገለግሉ ካህናት፤ እንዲሁም ከደብሩ መዘምራን የተወሰኑት ለዚሁ አገልግሎት ከአርብ ጃምሮ በቦታው በመድረስ ቫሳ በሚገኘው የፊንላንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ለምእመናኑ ቅዳሴ ትምህርትና ምክር አገልግሎት ተሰጥቷል። በተለይም ከቅዳሴው በኋላ በተካሄደው ጉባኤ ላይ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ቀሲስ ለማ በሱፈቃድ በዓሉን የተመለከተና ከምእመናን ሕይወት ጋር በማያያዝ ሰፋ ያለና መንፈሳዊና ማኅበራዊ ሕይወትን የሚያጠነክር ሰፋ ያለ ትምህርትና አባታዊ ምክር ሰጥተዋል። በጉዞው የተሳተፉ የመዝሙር ክፍል አባላትም የዝማሬ አገልግሎት አበርክተዋል። በመጨረሻም መዝሙር ከተዘመረና የመዝጊያ ጸሎት ከተደረገ በኋላ የበዓሉ ፍፃሜ ሆኗል። የቫሳ ከተማ ከሄልሲንኪ 423 ኪሎሜትር ያህል የምትርቅ መሆኗ ይታወቃል ።

የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በቫሳ

share

Comments

  1. መስረት ጥላሁን : December 26, 2017 at 1:29 pm

    እግዚአብሔር ይመስገን

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *