Uncategorized


24
Sep 2016
የመስቀል ደመራ ለመጀመሪያ ጊዜ በሂልሲንኪ ሊከበር ነው

በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ለመጀመሪያ ጊዜ የመስቀል ደመራን በዓል በሄልሲንኪ ከተማ የዮሐንስ ቤ/ክ አጠገብ በሚገኘው (korkeavuorenkatu 12) አደባባይ/ሜዳ/ ሰኞ መስከረም 16 ቀን 2009 ዓ.ም. ከ17፡30– 20፡30 ፣ የደመራ ሥነ ሥርዓት በማከናወን እንደሚያከብር ተገለጸ። የደመራ ሥነ ሥርዓቱ የደብሩ ካህናት፣ ዲያቆናት፣ መዘምራን፣ ሕጻናት፣ በሄልሲንኪና አጎራባች ከተሞች የሚገኙ ምእመናን፤ ተጋባዥ ካህናት፣ ዲያቆናት ፣ የፊንላንድ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሓላፊዎች ፣ የከተማው ከንቲባ ጽ/ቤት እና ልዩ ልዩ ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት እንደሚከናወን ታውቋል፡፡ የመስቀል ደመራ በዓል የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በአይሁድ አማካኝነት ተቀብሮ ከነበረበት ቦታ የንጉሥ ቆስጠንጢኖስ እናት የሆነቸው ንግሥት ዕሌኒ ፣ ደመራ......

Read More


29
Aug 2016
የጻድቁ አባታችን በዓለ ዕረፍት ተከብሮ ዋለ

በሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖትን የበዓለ ዕረፍታቸውን ዓመታዊ ክብረ በዓል ነሐሴ 22 ቀን 2008ዓ.ም. (28.08.16 እ.ኤ.አ) ፣ ቮሳሪ በሚገኘው የፊኒሽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የሶፊያ ማዕከል በርካታ ሕዝበ ክርስቲያን በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ዋለ፡፡ በበዓሉ ላይ መጋቤ ብሉይ ቀሲስ ለማ በሱ ፈቃድ የደብሩ አስተዳዳሪ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ፣ ቀሲስ አንገሶም በኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሄልሲንኪ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ፣ እና የደብሩ ዲያቆናትና ቀሳውስት መምህር ቀሲስ መንግስቱ ጎበዜ(ከስዊድን) ፣ ሊቀ መዘምራን ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ(ከኢትዮጵያ)፣ መምህር ፍቃዱ ሣህሌ(ከኢትዮጵያ) ፣ እንዲሁም ካህናት፣ ዲያቆናት፣ የሰንበት ት/ቤት መዘምራን፣ ሕጻናትና በፊንላንድ የሚገኙ የኢትዮጵያና......

Read More


29
Aug 2016
"ኢትዮጵያ ዛሬ" በሚል መሪ ቃል  ዐውደ ጥናት ተካሄደ

ነሐሴ 21 2008 ዓ.ም. (27.08.16 እ.ኤ.አ) በሶፈያ የባህል ማዕከል ”ኢትዮጵያ ዛሬ (Etiopia tänään)” በሚል መሪ ቃል በሶፍያ የባህል ማዕከል እና በፊኒሽ ኦርቶዶክስ አስተባባሪነት የተዘጋጀ ዐውደ ጥናት ተካሄደ። ዐውደ ጥናቱ የተለያዩ መርሀግብሮችን በማካተት ከቀኑ 12፡00 እስከ 18፡00 ቀጥሎ ውሏል። ከቀኑ 12-14 ሰዓት በዕለቱ በሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ጋባዥነት ከስዊድን የሉንድ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ መምህር ቀሲስ መንግስቱ ጎበዜ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ታሪክ በሚመለከት ጥናታዊ ጽሑፍ በማቅረብ ፣ በቦታው ለታደሙት የጉባኤው ተሳታፊዎች ሰፋ ያለ ግንዛቤ አስጨብጠዋል፡፡ በማስከተልም። ወ/ሪት ፌቨን ትዕግሥቱ “ቱሪዝም በኢትዮጵያ” በተሰኘ ርዕስ የኢትዮጵያን ዋና ዋና......

Read More


26
Aug 2016
አባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት በዓለ እረፍት የዋዜማ በዓል በድምቀት ተከበረ!

በፊላንድ ሄልሲንኪ አሉንኩላን ቤተክርስቲያን የአባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት በዓለ እረፍታቸውን አስመልክቶ የዋዜማ ጉባኤ የደብሩ አስተዳዳሪ ቀሲስ ለማ በሱፍቃድ ፤ ተጋባዥ እንግዶች መምህር ቀሲስ መንግስቱ ጎበዜ(ከስዊድን) ሊቀ መዘምራን ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ(ከኢትዮጵያ) መምህር ፍቃዱ ሣህሌ(ከኢትዮጵያ) ፣ የሰንበት ት/ቤቱ መዘምህራን እና ምዕመናን በተገኙበት በታላቅ መንፈሳዊ ስነ-ስርዓት ተከብሯል፡፡ ሕጻናትም በፕሮግራሙ ላይ ዝማሬን አቅርበዋል። በነገውም ዕለት ከቀኑ 12:00 ሰዓት እስከ 18:00 ሰዓት እንዲሁም ከምሽቱ 22:00 ሰዓት ጀምሮ በተለያዩ የአዳር መንፈሳዊ አገልግሎቶች በሶፊያ የባህል አዳራሽ እንደሚቀጥልም ተገልጾዋል። በዋዜማ ሌሊቱን በማህሌት በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን በጋራ በመሆን መንፈሳዊ አገልግሎት ይቀጥላል።...

Read More


18
Aug 2016
በቫሳ ለመጀመሪያ ጊዜ የቅዳሴና የሥርዐተ ጥምቀት አገልግሎት ተሰጠ

በቫሳና አካባቢው ለሚኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች እሑድ ነሐሴ 8 2008 ዓ.ም. ከሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ወደ ስፍራው በተጓዙ አገልጋዮች አማካኝነት ለመጀመሪያ ጊዜ የቅዳሴና የሥርዓተ ጥምቀት አገልግሎት ተከናውኗል፡፡ በዕለቱ በተካሄደው  መንፈሳዊ አገልግሎት በአካባቢው የሚገኙ የእምነቱ ተከታዮች የተሳተፉ ሲሆን ለሰባት ሕጻናትም  ሥርዓተ ጥምቀት ተፈፅሟል፡፡ ቫሳ ውስጥ መንፈሳዊ አገልግሎት በመደበኛ የሰንበት ጉባኤ አማካኘነት ላለፉት አራት ዓመታት ይሰጥ እንደነበርና፣ የቅዳሴ አገልግሎት ለማግኘት ግን ሕዝበ ክርስቲያኑ ወደ ሄልሲንኪ በመጓዝ  ወይም በሁለት ወር አንድ ጊዜ  በግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በሚዘጋጅ መንፈሳዊ አገልግሎት ይሳተፍ እንደነበር በአገልግሎቱ ላይ የተገኙ ምእመን ገልጸዋል፡፡ በአግልግሎቱ ላይ የተሳተፉ የአካባቢው ነዋሪዎች......

Read More


12
May 2016
የጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖትን በዓለ ፍልሠት ከአንድ ቀን  ዐውደ ርእይ ጋር ለማክበር ዝግጅት መጨረሱን አስታወቀ

በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ደብር ግንቦት 13/2008 ዓ.ም(May 21 2016) የጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖትን በዓለ ፍልሠት እንደሚከበር የደብሩ ጽ/ቤት አስታወቀ። በዓሉ በደብሩ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሚከበር የተገለጸ ሲሆን በዕለቱ “የእናት ቤተ ክርስቲያናችንን አደራ እንጠብቅ አንድነታችንንም አንተው” በሚል መሪ ቃል ልዩ የአንድ ቀን አውደ ርዕይ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሚያካሄድ የደብሩ አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ለማ በሱፍቃድ ገልጸዋል። አውደ ርዕዩም በአራት ትዕይንት የተከፈለ ሲሆን በተለያዩ መንፈሳዊ መርሐ ግብሮች በደመቀ ሁኔታ እንደሚታጀብ ተገልጾል። በፊንላንድ እና በአጎራባች ሀገሮች አድባራት የምትገኙ ምእመናን የበዓሉ በረከት ተሳታፊ እንድትሆኑና በዕለቱም ዐውደ ርእዩን እንድትጉበኙ የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት በጻድቁ ስም ጥሪውን ያስተላልፋል። ወስብሐት......

Read More


05
May 2016
የሄልሲን ደብረ አሚን አቡነ የተክለሃይማኖት ደብር በፊላንድ መንግስት እውቅና አገኘ!

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ደብር በፊላንድ መንግስት በቤተክርስቲያን ደረጃ ተመዝግቦ እውቅና መሰጠቱን የደብሩ አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ቀሲስ ለማ በሱፍቃድ አስታወቁ። የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ደብር በማኅበር ደረጃ ከ20 አመታት በላይ ማስቆጥሩ ይታወሳል፤ ይሁንና ላለፉት 5 ዓመት በቤተክርስቲያን ደረጃ ተመዝግቦ በፊንላንድ መንግሥት ዘንድ እውቅና ለማግኘት ከፍተኛ ጥረቶች መደረጋቸውን ተገልፇል። እንደ ደብሩ አስተዳዳሪ ቀሲስ ለማ ገለፃ የተደረጉት ጥረቶች በመጨረሻ ተሳክተው በፊንላንድ ሀገር የመጀመሪያው በሀገሪቱ መንግስት ዘንድ እውቅና የተሰጠው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ በሰሜን ምዕራብ አውሮፓ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን ተብሎ መመዝገቡን ተናገረዋል።......

Read More


30
Apr 2016
የስቅለት በዓል ዛሬ በደብራችን በድምቀት ተከብሮ ዋለ

የጌታችን እና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት በዓል ዛሬ በደብራችን በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ተከብሮ ውሏል፡፡ በዕለቱንም ከጠዋት ጀምሮ በርካታ ምእመናን በቤተ ክርስቲያን ተገኝተው ጌታችን ስለኛ ብሎ የተቀበለውን መከራና ስቃይ እያሰቡ በመጸለይና በመስገድ አሳልፈዋል፡፡ በደብሩ አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ቀሲስ ለማ በሱፍቃድም የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት የ5500 ዓመት የዕዳ ደብዳቤያችን የተደመሰሰበት የተወገደበት ፣ የሰው ልጅ የኃጢአት ቀንበር የተሰበረበት፣ የሞትና የጨለማ መጋረጃ የተቀደደበት፣ ፍፁም ፍቅር የተገለጠበት ዕለት መሆኑን አስተምረዋል፡፡ እኛም በየትኛውም ዓለም የምንኖር ምእመናን ከሁሉም በላይ የሚበልጠው ፍቅር ነውና ፍቅርን ገንዘብ እናድርግ በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ በማያያዝም ነገ ትንሣአኤ......

Read More