Uncategorized


13
Jun 2017
የተመራቂ ተማሪዎች ልዩ መርሃግብር ተካሄደ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አውሮጳ ሀገረ ስብከት በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ሰኔ ፬ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም (June 11, 2017) ዓ.ም በቀለም ትምህርታቸው ከተለያዩ የትምህርት ተቋማት ለተመረቁ ተማሪዎች ልዩ መርሃ ግብር ተዘጋጀ። በመርሃ ግብሩ መጀመሪያ በደብሩ የስብከተ ወንጌል ክፍል ተጠሪ በተላለፈው መልእክት በዘንድሮ ዓመት የተጀመረው ይህ የተመራቂዎች መርሃ ግብር ወደፊት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል። በተለያዩ የትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን የሚከታተሉ ተማሪዎች ከቀለም ትምህርት ጎን ለጎን መንፈሳዊውንም ትምህርት በሰንበት ትምህርት ቤት ተመዝግበው ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን ከዛሬ በኋላ ተመራቂዎቹ በእውቀታቸውና በመሳሰለው ሁሉ ቤተ ክርስቲያናቸውን እንዲያገለግሉ ጥሪ ቀርቧል ። መርሃ......

Read More


13
May 2017
የትንሣኤና የእመቤታችን የድንግል ማርያም የልደት በዓል ልዩ መርሐ ግብር በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አውሮጳ ሀገረ ስብከት በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በደብሩ ሰንበት ትምህርት ቤት  የሕፃናትና አዳጊዎች  ንዑስ ክፍል የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሣኤ በዓልና የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ ሚያዝያ 29 ቀን 2009 ዓ.ም. (May 7, 2017) ልዩ የሕፃናት እና የአዳጊ ልጆች መርሐ ግብር ተካሄደ።  በመርሐ ግብሩ መጀመሪያ ላይ ከሕፃናት እና አዳጊዎች ንዑስ ክፍል በተላለፈው መልእክት ሕፃናትና  አዳጊ ልጆች የነገ የቤተ ክርስቲያናችን ተረካቢዎች በመሆናቸው ይልቁንም በውጪው ዓለም ለሚገኙ ሕፃናትና አዳጊዎች  የበልጠ ትኩረት በመስጠት  ሃይማኖታቸውን ፣ ቋንቋቸውን እና በጎ ባህላቸውን እንዲያውቁ እና......

Read More


13
Apr 2017
የሆሣዕና በዓል በደማቅ ሁኔታ ተከበረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ሚያዚያ 1 ቀን 2009 ዓ.ም. የሆሣዕና በዓል በደማቅ ሁኔታ ተከበረ። በዕለቱም በየዓመቱ እንደሚከናወነው ሁሉ ቅዳሴ ሥርዓቱ በተለየ ሁኔታ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ቀኖና መሠረት ከተከናወነ በኋላ በቀሲስ ዶክተር አምሳሉ ተፈራ ስለ ሆሣዕና በዓል አጠር ያለ ትምህርት ተሰጥቷል፡፡ የሆሣዕና በዓል ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ አዕሩግም ሕፃናትም ‹‹ ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ፣ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው ፣ሆሣዕና በአርያም›› እያሉ ጌታችንን በክብር መቀበላቸው የሚታወስበት በዓል መሆኑን፤ ‹ሆሣዕና› የሚለው ቃል ‹ሆሼዕናህ› ከሚለው የዕብራይስጥ ቃል የተወሰደ ሲሆን ፣......

Read More


13
Apr 2017
በሶፊያ ባህል ማዕከል ልዩ ዐውደ ጥናት ተካሄደ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን እና በፊንላንድ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የሶፊያ ባህል ማዕከል ትብብር ቅዳሜ መጋቢት 30 ቀን 2009 ዓ.ም. በሶፊያ የባህል ማዕከል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ገዳማትን እና የቅዱስ ያሬድን ዜማ በሚመለከት ልዩ ዐውደ ጥናት ተካሄደ፡፡ በዐውደ ጥናቱም ላይ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ለማ በሱፈቃድ፣ የአጥቢያው ምእመናን፣ የፊንሽ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አባቶች እና የሀገሪቱ ዜጎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ በመጀመሪያ ገዳማዊ ሕይወት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሚል ርዕስ የገዳማዊ ሕይወት አጀማመር፣ ያበረከተው አስተዋጽዖ እና......

Read More


09
Feb 2017
የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ሁለት የወረዳ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤቶችን አዋቀረ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት የወረዳ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤቶችን አዋቀረ። ሀገረ ስብከቱ የመላው አውሮፓ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ ሙሴ መቀመጫ በሆነችው በጀርመን ሀገረ በምትገኘው የሮሰልስሃይም ከተማ ጥር 19 እና 20 ቀን 2009 ዓ.ም ጉባኤውን አካሂዷል። በጉባኤው ላይ የአህጉረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ፣ በሸንገን ስቴት ውስጥ ባሉ የአውሮፓ ሀገራት ያሉ የሀገረ ስብከቱ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎች እና ተወካዮች የተገኙ ሲሆን በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችንም አሳልፏል። ብፁዕ ሊቀ ጳጳሱ በጉባኤው መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት መልእክት በሀገረ ስብከቱ ውስጥ ስብከተ ወንጌልን ለማስፋፋት እና የቤተ ክርስቲያንን......

Read More


25
Jan 2017
በዓለ ጥምቀት በደማቅ ሁኔታ ተከበረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አውሮጳ ሀገረ ስብከት በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ጥር 13 ቀን የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት ቲኩሪላ በሚገኘው በፊኒሽ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በደማቅ ሁኔታ ተከበረ። በዕለቱ በተያዘው መርሃ ግብር መሠረት ሥርዓተ ቅዳሴው ከተከናወነ በኋላ የባህረ ጥምቀቱ ሥርዓተ ጸሎት ተደርሶ ህዝቡም ጸበል ተረጭቶ የበረከቱ ተካፋይ ሆኗል፡፡በመቀጠልም በደብሩ መዘምራን ዕለቱን የተመለከተ  ያሬዳዊ ዜማ የቀረበ ሲሆን  በመጨረሻም በደብሩ አስተዳዳሪ በመጋቤ ብሉይ ቀሲስ ለማ በሱፈቃድ   ትምህርተ  ወንጌል  እና ጸሎተ ቡራኬ ከተሰጠ በኋላ  የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል።...

Read More


22
Jan 2017
የልደትን በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ የሕጻናት መርሐ ግብር ተካሄደ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አውሮጳ ሀገረ ስብከት በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤት ክፍል የሕፃናትና  አዳጊ ንዑስ ክፍል የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል ምክንያት በማድረግ እሑድ ታኅሣሥ 30 ቀን 2009 ዓ.ም (January 8, 2017) ከሰዓት በኋላ ልዩ የሕጻናት እና የአዳጊ ልጆች መርሐ ግብር ተካሄደ። በመርሐ ግብሩ መጀመሪያ ላይ ከሰንበት ትምህርት ቤቱ በተላለፈው መልእክት ሕፃናትና  አዳጊ ልጆች የነገ የቤተ ክርስቲያናችን ተረካቢዎች በመሆናቸው  ትኩረት፣ ፍቅርንና ጊዜን ሰጥተን መሥራት የሚጠበቅብን መሆኑን እና ጥሩ ምሳሌ መሆን ከሁሉም ምእመናን የሚጠበቅ መሆኑ ተገልጿል። ይህን መሰል ልዩ መርሐ ግብር ለልጆች......

Read More


03
Jan 2017
የ2009 ዓ.ም. የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በዓለ ልደት ተከበረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት በሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት  ቤተ ክርስቲያን ታኅሣሥ 24 ቀን የሚውለውን የጻድቁ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን በዓለ ልደት ታኅሣሥ 22 ቀን 2009 ዓ.ም. ቲኩሪላ በሚገኘው የፊንላንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን  ተከበረ። በዓሉ ታኅሣሥ 21 ቀን 2009 ዓ.ም. ምሽት ጀምሮ፣ የደብሩ አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ቀሲስ ለማ በሱፈቃድ፣  የደብሩ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን፣ ሕጻናት፣ ከሄልሲንኪና እና ከተለያዩ ከተሞች የመጡ ምእመናን እና ምእመናት እንዲሁም በፊንላንድ የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኤርትራ ኦርቶዶክስ  ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናት እና ምዕመናን በተገኙበት ተከብሯል። በዓሉ ዓርብ ምሽት በጸሎት ከተጀመረ በኋላ የአቡነ ተክለ......

Read More


29
Sep 2016
የመስቀል ደመራ በዓል ለመጀመሪያ ጊዜ በድምቀት ተከበረ

በፊንላንድ ሄልሲንኪ ከተማ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን አደባባይ. /ሜዳ / ላይ በተካሄደው የደመራ ሥነ ሥርዓት፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ቀሲስ ለማ በሱፈቃድ፣ የሄልሲንኪ ከተማ ምክትል ከንቲባ ሪትቫ ቪልያነን ፣ የደብሩ ዲያቆናት ፣ የሄልሲንኪ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ካህናት ዲያቆናት እና ምእመናን ፣ ጥንግ ድርብ የለበሱ የደብሩ መዘምራን፣ ሕጻናት፣ ከሄልሲንኪና ከአጎራባች ከተሞች የመጡ ምእመናን፣ የባህል እና የሌሎች ተቋማት ሓላፊዋች ፣ጋዜጠኞች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት መስከረም 16 ቀን 2009 ዓ.ም. ከ 17፡30 – 20፡30 በተካሄደ የመስቀል ደመራ ሥነ ሥርዓት በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል። ሥነ......

Read More