Monthly Archives: January 2019


22
Jan 2019
ከሲኖዶሳዊ አንድነቱ በኋላ የመጀመሪያው የጥምቀት እና የቃና ዘገሊላ በዓል በፊንላንድ ሄልሲንኪ ከተማ በጋራ ተከበረ

ከሲኖዶሳዊ ዕርቅና ሰላም በኋላ የመጀመሪያው በዓለ ጥምቀት በሰሜን አውሮፓ በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ÷ ጥር 11 ቀን 2011 ዓ.ም በጋራ ተከበረ፡፡ የበዓሉ የአከባበር ሥነ ሥርዐት እና ጸሎተ ቅዳሴው በደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያ አስተዳዳሪ ÷ በመልአከ አሚን ቀሲስ ለማ በሱ ፈቃድ እየተመራ ÷ከተለያዩ የፊንላንድ ከተሞች የመጡ ኦርቶዶክሳውያን በተገኙበት በጸሎተ ቅዳሴና በትምህርተ ወንጌል በድምቀት ተከብሯል፡፡ በተዘጋጀው የባሕረ ጥምቀት ሥፍራ ስብሐተ እግዚአብሔር ደርሶ፣በሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ዕለቱን የሚያዘክር ወረብ ቀርቦና ከኢትዮጵያ በመጡት መምህር ÷በዲያቆን ታደሰ ወርቁ በዓሉን የተመለከተ ትምህርት ከተሰጠ በኋላ የበዓሉ ፍጻሜ መሆኑ ተዘግቧል፡፡ ከዚሁ ጋራ......

Read More