Daily Archives: April 7, 2016


07
Apr 2016
የእውነተኛዋ ቤተ ክርስቲያን መገለጫዎች

በቀሲስ ብርሃኑ ጎበና ቤት የሚለው ቃል ወገን፤ ነገድ፤ ዘር፤ ትውልድ፤ ጉባኤ፤ ማኅበር ማለት እንደሆነ አለቃ ኪዳነወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላት መጽሐፋቸው ላይ ጠቅሰዋል፡፡(ኪ.ወ.ክ ገጽ 268) የያዕቆብ ወገን ቤተ ያዕቆብ (ቤተ እስራኤል)፤የዳዊት ወገን ቤተ ዳዊት እንዲባል በመንፈሳዊና በምሥጥራዊ ልደት ከክርስቶስ የተወለዱ ምእመናንም ቤተ ክርስቲያን ይባላሉ፤ ቤተ ክርስቶስ (የክርስቶስ ወገን) እንደ ማለት ነው፡፡ ዳሩ ግን በዘመናችን ስምና ግብር ለየቅል ሆነው በተቃራኒ ያሉት ወገኖች ሳይቀሩ ስሙን መጠሪያ አድርገው አናስተውላለን፤ ዘመናችን አማናዊቱ ቤተ ክርስቲያን ስምዋን ወስደው በሚጠሩ አስመሳዮች የተወረረችበት ወቅት በመሆኑ እውነተኛዋን ለይቶ ማወቅ ግድ ይላል፡፡ እንዲት ቤተ ክርስቲያንን ቤተ ክርስቲያን ዘክርስቶስ የሚያሰኛት በ381 ዓ.ም በቁስጥንጥንያ የተሰበሰቡት......

Read More


07
Apr 2016
ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

እግዚአብሔር አምላክ ይህንን ዓለም ካለመኖር ወደ መኖር ሲያመጣው ከተፈጠረበት ሥርዓት ጋር ነው። የዓለም ተፈጥሮም ያለ ሥርዓት ትርጉም የለውም። ፍጥረት ሁሉ እግዚአብሔርን ከሚያደንቅበት ነገር አንዱ የተሰጠውን ሥርዓት ጠብቆ መጓዙ ነው። ወንዞች ወደ ዝቅተኛ ስፍራ ይፈስሳሉ፣ አራዊት በሌሊት ይወጣሉ፣ ሰዎች ተግባራቸውን በቀን ያከናውናሉ፣ ፀሐይ በምሥራቅ ትወጣለች። ይህ ሁሉ የሚያስተምረን ሥርዓት ከጥንተ ፍጥረት ጀምሮ የነበረና ወደፊትም የሚቀጥል መሆኑን ነው። መዝ ፩፻፫፡ ፮-፳፭። ሥርዓት ሠርዐ ከሚለው የግእዝ ግሥ የወጣ ስም ነው። ትርጉሙም ደምብ አሠራር ማለት ነው። ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንም ስንል የቤተ ክርስቲያን መገልገያ ደንብ ማለታችን ነው። አምልኮተ እግዚአብሔር የሚከናወንባት ቤተ ክርስቲያን ምስጢራዊና መንፈሳዊ ሥርዓት አላት። መንፈሳዊ......

Read More


07
Apr 2016
ሰማዕትነት

ሰማዕት ‹‹ሰምዐ›› ከሚል የግእዝ ቃል የተወሰደ ሲሆን፤ ትርጉሙም ያየነውን፣ የሰማነውን መመስክር መቻል እንደሆነ የኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፈ ስዋስወ ወግስ መዝገበ ቃላት ገጽ 671 ይነግረናል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ‹‹እኔ ለእውነት ለመመስከር መጥቻለሁ›› በማለት እውነትን እንድንመሰክር አብነት ሆኖናል /ዮሐ.18፥37/፡፡ ሰማዕትነት በሃይማኖታዊ ትርጉሙ ስንመለከተው ስለ እግዚአብሔር፣ ስለቅድስት ቤተክርስቲያን፣ ስለ ሃይማኖታቸው በእውነት በመመስከራቸው ጀርባቸውን ለግርፋት፣ ሰውነታቸውን ለእሳት፣ እግራቸውን ለሰንሰለት፣ አንገታቸውን ለስለት አሳልፈው ለሰጡ፤ በድንጊያ ተወግረው በመንኮራኩር ተፈጭተው በጦር ተወግተው አልያም በግዞትና በስደት በዱር በገደል ተንከራተው ለዐረፉ ቅዱሳን አባቶችና ቅዱሳት እናቶች የሚሰጥና ተጋድሎአቸውን ጠቅለል አድርጎ የሚገልጽ ቃል ነው፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊው እመቤታችንን ባመሰገነበት ድርሳኑ “ሰማዕታት የዚህችን......

Read More


07
Apr 2016
ምሥጢረ ሥላሴ - ክፍል ፪

ሐዋርያዊት የሆነች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከዘመነ ሐዋርያት ጀምሮ ክርስቲያናዊ ትውፊታዋንና ኀይማኖታዊ አስተምህሮዋን ጠብቃ የኖረች ናት ። ከአስተምህሮዋም አንዱና ዋንኛው ምሥጢረ ሥላሴ ነው ። ምሥጢረ ሥላሴ ( የእግዚአብሔር ባሕርይ ) ምሉዕና ስፉሕ ረቂቅና ምጡቅ የሆነ ተመጣጣኝ ምሳሌ የማይገኝለት ቢሆንም ፣ ቅዱሳን ነቢያትና ቅዱሳን ሐዋርያት በመንፈሰ እግዚአብሔር እየተመሩ የጻፏቸውን መጻሕፍተ ብሉያትንና መጻሕፍተ ሐዲሳትን ምስክር በማድረግ አበው ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንደ አስተማሩን ፣ (በምሳሌ ዘየሐጽጽ) ደካማው አዕምሯችን በሚረዳው ዕኛ በምናውቀው ለሥላሴ ተመጣጣኝ ባልሆነ በአነስተኛ ምሳሌ እየመሰልን የእግዚአብሔርን አንድነትና ሦስትነት በዕርሱ አጋዥነትና ረዳትነት ለመጻፍ እጀምራለሑ ፡፡ ሰውን በአርዓያችንና በአምሳላችን እንፍጠር ነቢይ ሙሴ በጻፈው......

Read More


07
Apr 2016
ምሥጢረ ሥላሴ - ክፍል ፩

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዓለም ከመፈጠሩ በፊት የነበረ፤ ያለና የሚኖር አንድ አምላክ መኖሩን ታምናለች፡፡ ይኸውም አንድ አምላክ፤ በአካል፤ በስም፣ በግብር ሦስት፤ በመለኮት አንድ የሆነ አንድ እግዚአብሔር አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ መሆኑን አምና ታሳምናለች፤ ተምራ ታስተምራለች፡፡ ስለ እግዚአብሔር አንድነትና ሦስትነት፤ ፈጣሪነትና መጋቢነት… የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ባላት ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ መሰረት ከአምስቱ አእማደ ምሥጢር አንደኛውን ክፍል ምሥጢረ ሥላሴን እንመለከታለን፡፡ ሥላሴ ማለት ሠለሰ ሦስት አደረገ ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተወሰደ ሲሆን ትርጓሜውም ሦስት ሦስትነት ማለት ነው፡፡ ሥሉስ ቅዱስ ማለት ደግሞ ልዩ ሦስት ማለት ነው፡፡ ልዩነቱም የአካል ሦስትነት ካላቸው የህልውና አንድነት ከሌላቸው ከአብርሃም፣ ከይስሐቅና ከያዕቆብ......

Read More


07
Apr 2016
ነገረ ማርያም

ርዕሱን ወደተመለከተው ወደ ዋናው ትምህርት ከመግባታችን አስቀድሞ የርዕሱን ትርጉም ማወቅ ይቀድማልና ነገረ ማርያም የሚለውን ትርጉም እናያለን። ነገረ ማርያም ማለት የእመቤታችንን ነገር (ስለ እመቤታችን) የሚያወሳ ነገር ወይም ትምህርት ማለት ነው። ይህም አስቀድማ በአምላክ ሕሊና መታሰቧን፣ ትንቢት የተነገረላት፣ ምሳሌ የተመሰለላት መሆኗን፣ ልደቷን፣ እድገቷን፣ አምላክን ፀንሳ መውለዷን ዕረፍቷን፣ ትንሣኤዋን ወዘተ የሚተርክ የሚያስተምር ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ማርያም በሚል ስም የሚጠሩ ብዙ ሴቶች አሉ። እነዚህም በብሉይና በሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ላይ ተጠቅሰው ይገኛሉ። እነርሱም፡- 1ኛ. የሙሴ እህት ማርያም፡- ይህች ማርያም ሙሴ በወንዝ ዳር በተጣለ ጊዜ በእርሱ ላይ የሚሆነውን ነገር ስትከታተል ነበር። ዘፀ.2፥4-8 – እስራኤል ባሕረ ኤርትራን ሲሻገሩ......

Read More


07
Apr 2016
ነትገ ማይ አይኅ

”ወበጽርሑሰ ኵሉ ይብል ስብሐት እግዚአብሔር ያስተጋብኦ ለማየ አይኅ ሁሉም በመቅደሱ፦ ምስጋና ይላል እግዚአብሔር የጥፋት ውሃን ሰብስቧልና” መዝ ፳፰፥፱ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በዚህ መዝሙሩ ላይ፦ ምዕመናን ለአምላካቸው የአምልኮ መገለጫ የሆኑትን ምስጋናና ስግደት ሊያደርጉ እንደሚገባቸው በመጀመሪያዎቹ ስንኞች ላይ አስፍሯል፦ ”በቅድስናው ስፍራ ለእግዚአብሔር ስገዱ” – እንዲል። በሚቀጥሉት ስንኞች ደግሞ እግዚአብሔር ሁሉን ቻይ አምላክ እንደሆነ ሰብኳል። ”የክብር አምላክ አንጐደጐደ” በማለት በብዙ ምሳሌ አስተምሯል፤ የሊባኖስ ዝግባን፣ ውሃን፣ እሳትን፣ የቃዴስን ምድረ በዳ እየጠቀሰ ተናግሯል። ይህ ሁሉ የእስራኤላውያን የአምልኮ ታሪክና የእግዚአብሔርን ተአምራት የሚያስታውስ ነው፤ ይህውም በምድረ በዳ እና በመሳፍንት ዘመን ሁሉ የነበረው ነው፦ ውሃውን ያለ ግድብ ሲያቆም፣ ከጭንጫ ሲያፈልቅ፣......

Read More


07
Apr 2016
ጸሎት ክፍል 2

በመ/ር ምሥጢረ ሥላሴ ማናየ “አንትሙሰ ሶበት ጸልዩ ስመ ዝበሉ፡፡” ማቴ.6፥ እናንተስ በምትጸልዩበት ጊዜ እንዲህ በላችሁ ጸልዩ “አባታችን ሆይ በሰማያት የምትኖር ስምህ ይቀደስ መንግሥትህ ትምጣ ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነ እንዲሁ በምድር ይሁን…. በዚህ የጸሎት ክፍል ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከ81 መጻሕፍት የተገኙ አምስት ቁም ነገሮችን አስተምሯል፡፡ ሃይማኖት ተስፋ ፍቅር ትሕትና ጸሎት 1.   ሃይማኖት፡- ሃይማኖት ማለት በዐይናችን ያላየነውን አምላክ አባታችን ሆይ ሲሉ መኖር ነው ቀደም ሲል የነበሩ አበው ነቢያት ሲጸልዩ እግዚእነ አምላክነ ንጉሥነ እያሉ ይጸልዩ ነበር፡፡ ይህም ከግብርናተ ዲያብሎስ /ለዲያብሎስ ከመገዛት/ እንዳልዳኑ ለማጠየቅ ነው፡፡ እኛን ግን ከግብርናተ ዲያብሎስ ነጻ አውጥቻችኋለሁ ሲል አባታችን ሆይ......

Read More


07
Apr 2016
ጸሎት ክፍል 1

በመ/ር ምሥጢረ ሥላሴ ማናየ ጸሎት ጸለየ፡- ለመነ፣ ጠየቀ አማለደ፣ ማለደ ካለው የግዕዝ ቃል የወጣ ቃል ነው፡፡ ጸሎት ማለት ጠቅለል አድርገን ስንመለከተው ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር እግዚአብሔርን ማመስገን መለመን፣ መጠየቅ፣ መማለድ፣ መማፀን ነው፡፡ “ጸሎት ብሂል ተናግሮ ምስለ እግዚአብሔር፡፡” አባታችን አዳምም ከመላእክት ተምሮ በየሰዓቱ ይጸልይ ያመሰግን ነበር፡፡ ዲያብሎስ በእባብ አድሮ ወደ አዳም በመጣ ጊዜ ጸሎት እያደረገ ስለነበር ዲያብሎስን ድል ነሥቶታል ሔዋንን ግን ሥራ ፈትታ እግሯን ዘርግታ ስለአገኛት ድል ነስቷታል፡፡ ጸሎት ሰማእታት ከነደደ እሳት፣ ከተሳለ ስለት፣ ከአላውያን መኳንንት፣ ከአሕዛብ ነገሥታት ከዲያብሎስ ተንኮል እና ሽንገላ ዲያብሎስ በእነርሱ ላይ ከአጠመደው አሽከላ የዳኑበት ጋሻ ነው፡፡ ኤፌ.6፥10 21 ጸሎት፣ ሰው......

Read More


07
Apr 2016

በዲ/ን ኅብረት የሺጥላ ኪዳን የሚለው ቃል ‹‹ቃል›› ከሚለው ጋር እየተዛረፈ በብሉይ ኪዳን ለ280 ጊዜ ያህል ሲጠቀስ በአዲሰ ኪዳን ደግሞ ከ32 ጊዜ በላይ ተጠቅሷል፡፡ ‹‹ኪዳን›› ቃሉ ‹‹ተካየደ›› ተማማለ፣ ቃል ተገባባ ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ነው፡፡ ‹‹ምሕረት›› የሚለው ቃል ደግሞ ማብራሪያ ሳያሻው ምሥጢሩ ከነዘይቤው ከግእዝ የተወረሰ ነው፡፡ ስለዚህ ኪዳነ ምሕረት ማለት የምሕረት፣ የይቅርታ ውል፣ ስምምነት፣ መሐላ ማለት ነው፡፡ ኪዳን ከተራ ውሎችና ስምምነቶች የበለጠ ጽኑና ቀዋሚ ነው፡፡ ከፍ ያለ ክብደትም አለው፡፡ ‹‹ከመረጥኳቸው ጋር ቃል ኪዳኔን አድርጋለሁ›› ተብሎ በዳዊት መዝሙር እንደተጻፈ እግዚአብሔር ከመረጣቸው ቅዱሳኑ ሁሉ ጋር ቃል ኪዳን አድርጓል፡፡ ወደፊትም ያደርጋል፡፡ (መዝ88.3) ቃል ኪዳኑም የምሕረት ቃል......

Read More