Daily Archives: April 24, 2016


24
Apr 2016
ቤተ ክርስቲያናች በዛሬው ዕለት አዲስ ድረ ገጽ  አስመረቀች

የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክርለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በዛሬው ዕለት አዲስ ድረ ገጽ  አስመረቀች። በድረ ገጽ ስም www.teklehaymanot.fi በመባል የተሰየመውን ድረ ገጽ መርቀ የከፈቱት የደብሩ አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ቀሲስ ለማ በሱፍቃድ ሲሆኑ የተሠራው ሥራ እጅግ ዘመናዊና ሁሉን ያካተተ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ለምረቃ የበቃው ድረ ገጽ የተሰራው በቤተ ክርስቲያኗ መረጃና ግንኙነት ክፍል ሲሆን እስካሁን የአራት ወር ጊዜ እንደፈጀ ታውቋል። በአሁን ሰዓት ገጹ ላይም የዜና እና መርሐ ግብር፣ የህብር ሚዲያ፣ የህጻናት፣ ትምህርተ ሃይማኖት፣ ስርዓተ ቤተክርስቲያን እና ሌሎች አምዶች አሉት። በምረቃው ላይ ስለ ድረ ገጽ ትንታኔ የሰጠው የመረጃና ግንኙነት ክፍል አገልጋይ ወንድማችን ካቢናድ ተሻገር እንደተናገረ ይህ......

Read More


24
Apr 2016
ሆሣዕና ዕለት ከተፈጸሙት ተግባራት ምን እንማራለን?

ፍጹም ትህትናን ነብዩ ኢሳይያስ ”እግዚአብሔርን በረጅምና ከፍ ባለ ዙፋን ላይ ተቀምጦ አየሁት፥ የልብሱም ዘርፍ መቅደሱን ሞልቶት ነበር”(ኢሳ 6፥1)። ብሎ የተናገረለት የጌቶች ጌታ የንጉሦች ንጉሥ የሆነ አምላክ ራሱን ዝቅ አድርጎ በአህያ ጀርባ መቀመጡ ፍጹም ትህትናን ያስተምረናል። በከበረ ቃሉ ”ከእኔ ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ” (ማቴ 11᎓29) እንዳለን የከበረች ትህትናን ከባለቤቱ መማር ይገባናል። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለጌታ ትህትና የተናገረውንም ማስተዋል ይገባል ”እርሱ አምላካችን የሁሉ ፈጣሪና የማይመረመረ ክብር ያለው ንጉሥ ሆኖ ሳለ ለክብሩ በሚገባ ባማረና በተንቆጠቆጠ ቤት አልተወለደም ራሱን ዝቅ አድርጎ በበረት ተገኘ እንጂ። በዚህ ዓለም ባለጠግነትና ብዕል ከተትረፈረፈች እናት አልተወለደም......

Read More


24
Apr 2016
በዕለተ ሆሣዕና ለምን ዘንባባ ይዘን እንዘምራለን?

1- ይስሐቅ በተወለደ ጊዜ አብርሃም ደስ ብሎት ዘንባባ ይዞ እግዚአብሔርን አመስግኖበታል (የደስታ መግለጫ በመሆኑ አንተ ደስታ የምትሰጥ ሃዘናችንንም የምታርቅ አምላክ ነህ ሲሉ ነው) 2- ዘንባባ ደርቆ እንደገና ህይወት ይዘራል የደረቀ ሕይወታችንን የምታለመልም አምላክ ነህ ሲሉ ነው 3- ዘንባባ የሰላም ምልክት ነው የሰላም አምልክ ነህ ሲሉ ነው 4- ዘንባባ እሾሃማ ነው አንተ ህያው አሸናፊ አምላክ ነህ ሲሉ ነው 5- ዘንባባ እሳት አይበላውም ለብልቦ ይተወዋል እንጅ ጌታም አንተ ባህርይህ የማይመረመር ነው ሲሉ ነው 6- ዘንባባ የነፃነት ምልክት ነው ከባርነት ነፃ የምታወጣን አንተነህ ሲሉ ነው አኛም ይህን በማሰብ ዘንባባ ይዘን ሆሳእና በአርያም እያልን እለቱን እናስባለን፡፡...

Read More