25
Apr 2016
በቅዱስ ማርቆስ ወንጌል እንደተገለጠልን ጌታችን የሆሣዕና ዕለት ቢታንያ በምትባል መንደር ያድርና በማግስቱም ወደ ኢየሩሳሌም ሲሄድ ተራበ ፡፡/ማር. 11.11-14/ ቅጠል ያላትን በለስ ከሩቅ አይቶ ወደ በለሲቱ ቀረበ፣ ነገር ግን ከቅጠል በቀር አንዳች ፍሬ አላገኘባትም፡፡ ከአሁን ጀምሮ ማንም ከአንቺ ፍሬ አይብላ ብሎ ረገማት፡፡ በዚህ ምክንያት ይህ ዕለት መርገመ በለስ የተፈጸመበት ሰኞ ይባላል፡፡ ትርጓሜ፤- በለስ የተባለች ቤተ እስ ራኤል ናት፤ ፍሬ የተባለች፣ ሃይማኖትና ምግባር ናት፡፡ ከእስራኤል ፍቅርን፣ ሃይማኖትን፣ ምግባርን ፈለገ አላገኘም፡፡ እስራኤልን ሕዝበ እግዚአብሔር መባ ልን እንጂ፣ ነቢይነት፣ ካህንነት፣ መሥ ዋዕት አይገኝብሽ ብሎ ረገማት፡፡ በመርገሙ ምክንያት ትንቢት ክህነት መሥዋዕት ከቤተ እስራኤል ጠፉ፡፡ በለስ ኦሪት ናት፡- ኦሪትን......
Read More