Start Blog Type 1 (Full Width Image) and Sidbar

07
Apr 2016
ሰማዕትነት

ሰማዕት ‹‹ሰምዐ›› ከሚል የግእዝ ቃል የተወሰደ ሲሆን፤ ትርጉሙም ያየነውን፣ የሰማነውን መመስክር መቻል እንደሆነ የኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፈ ስዋስወ ወግስ መዝገበ ቃላት ገጽ 671 ይነግረናል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ‹‹እኔ ለእውነት ለመመስከር መጥቻለሁ›› በማለት እውነትን እንድንመሰክር አብነት ሆኖናል /ዮሐ.18፥37/፡፡ ሰማዕትነት በሃይማኖታዊ ትርጉሙ ስንመለከተው ስለ እግዚአብሔር፣ ስለቅድስት ቤተክርስቲያን፣ ስለ ሃይማኖታቸው በእውነት በመመስከራቸው ጀርባቸውን ለግርፋት፣ ሰውነታቸውን ለእሳት፣ እግራቸውን ለሰንሰለት፣ አንገታቸውን ለስለት አሳልፈው ለሰጡ፤ በድንጊያ ተወግረው በመንኮራኩር ተፈጭተው በጦር ተወግተው አልያም በግዞትና በስደት በዱር በገደል ተንከራተው ለዐረፉ ቅዱሳን አባቶችና ቅዱሳት እናቶች የሚሰጥና ተጋድሎአቸውን ጠቅለል አድርጎ የሚገልጽ ቃል ነው፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊው እመቤታችንን ባመሰገነበት ድርሳኑ “ሰማዕታት የዚህችን......

Read More


07
Apr 2016
ምሥጢረ ሥላሴ - ክፍል ፪

ሐዋርያዊት የሆነች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከዘመነ ሐዋርያት ጀምሮ ክርስቲያናዊ ትውፊታዋንና ኀይማኖታዊ አስተምህሮዋን ጠብቃ የኖረች ናት ። ከአስተምህሮዋም አንዱና ዋንኛው ምሥጢረ ሥላሴ ነው ። ምሥጢረ ሥላሴ ( የእግዚአብሔር ባሕርይ ) ምሉዕና ስፉሕ ረቂቅና ምጡቅ የሆነ ተመጣጣኝ ምሳሌ የማይገኝለት ቢሆንም ፣ ቅዱሳን ነቢያትና ቅዱሳን ሐዋርያት በመንፈሰ እግዚአብሔር እየተመሩ የጻፏቸውን መጻሕፍተ ብሉያትንና መጻሕፍተ ሐዲሳትን ምስክር በማድረግ አበው ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንደ አስተማሩን ፣ (በምሳሌ ዘየሐጽጽ) ደካማው አዕምሯችን በሚረዳው ዕኛ በምናውቀው ለሥላሴ ተመጣጣኝ ባልሆነ በአነስተኛ ምሳሌ እየመሰልን የእግዚአብሔርን አንድነትና ሦስትነት በዕርሱ አጋዥነትና ረዳትነት ለመጻፍ እጀምራለሑ ፡፡ ሰውን በአርዓያችንና በአምሳላችን እንፍጠር ነቢይ ሙሴ በጻፈው......

Read More


07
Apr 2016
ምሥጢረ ሥላሴ - ክፍል ፩

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዓለም ከመፈጠሩ በፊት የነበረ፤ ያለና የሚኖር አንድ አምላክ መኖሩን ታምናለች፡፡ ይኸውም አንድ አምላክ፤ በአካል፤ በስም፣ በግብር ሦስት፤ በመለኮት አንድ የሆነ አንድ እግዚአብሔር አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ መሆኑን አምና ታሳምናለች፤ ተምራ ታስተምራለች፡፡ ስለ እግዚአብሔር አንድነትና ሦስትነት፤ ፈጣሪነትና መጋቢነት… የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ባላት ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ መሰረት ከአምስቱ አእማደ ምሥጢር አንደኛውን ክፍል ምሥጢረ ሥላሴን እንመለከታለን፡፡ ሥላሴ ማለት ሠለሰ ሦስት አደረገ ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተወሰደ ሲሆን ትርጓሜውም ሦስት ሦስትነት ማለት ነው፡፡ ሥሉስ ቅዱስ ማለት ደግሞ ልዩ ሦስት ማለት ነው፡፡ ልዩነቱም የአካል ሦስትነት ካላቸው የህልውና አንድነት ከሌላቸው ከአብርሃም፣ ከይስሐቅና ከያዕቆብ......

Read More


07
Apr 2016
ነገረ ማርያም

ርዕሱን ወደተመለከተው ወደ ዋናው ትምህርት ከመግባታችን አስቀድሞ የርዕሱን ትርጉም ማወቅ ይቀድማልና ነገረ ማርያም የሚለውን ትርጉም እናያለን። ነገረ ማርያም ማለት የእመቤታችንን ነገር (ስለ እመቤታችን) የሚያወሳ ነገር ወይም ትምህርት ማለት ነው። ይህም አስቀድማ በአምላክ ሕሊና መታሰቧን፣ ትንቢት የተነገረላት፣ ምሳሌ የተመሰለላት መሆኗን፣ ልደቷን፣ እድገቷን፣ አምላክን ፀንሳ መውለዷን ዕረፍቷን፣ ትንሣኤዋን ወዘተ የሚተርክ የሚያስተምር ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ማርያም በሚል ስም የሚጠሩ ብዙ ሴቶች አሉ። እነዚህም በብሉይና በሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ላይ ተጠቅሰው ይገኛሉ። እነርሱም፡- 1ኛ. የሙሴ እህት ማርያም፡- ይህች ማርያም ሙሴ በወንዝ ዳር በተጣለ ጊዜ በእርሱ ላይ የሚሆነውን ነገር ስትከታተል ነበር። ዘፀ.2፥4-8 – እስራኤል ባሕረ ኤርትራን ሲሻገሩ......

Read More


Social Icons

Calendar

May 2024
M T W T F S S
 12345
6789101112
13141516171819
20212223242526
2728293031  

instagram

    flickr

    instagram