07
Apr 2016
ዳግም ምጽአት ‹‹ደገመ›› እና ‹‹መጽአ›› ከሚሉ ሁለት የግዕዝ ግሦች የተዋቀረ ሐረግ ነው፡፡ የጌታችንንና የአምላካችንን ለሁለተኛ ጊዜ ወደዚህች ዓለም መምጣት ያመለክታል፡፡ የክርስቶስ ዳግም ምጽአት ዳግምነቱ ለልደቱ ነው፡፡ ማለትም ልደቱን ‹‹ቀዳማዊ ምጽአት›› ካልን ዘንድ ለፍርድ መምጣቱን ‹‹ዳግም ምጽአት›› እንላለን፡፡ ‹‹ዳግም›› የሚለውን ቃል አንድ ነገር ያለ ምንም ለውጥ ወይም ልዩነት ሲደገም የምንጠቀምበት ከሆነ ‹‹የተካከለ ዳግም›› እንለዋለን፡፡ ያ ነገር መሠረታዊ ጭብጡን ሳይለቅ ነገር ግን በበርካታ ለውጦች ታጅቦ ከተደገመ ወይም ከቀደመው ጋር ሲነጻጸር ተደገመ የሚያሰኝ ምሥጢራዊ አካሄድ ካለው ‹‹ያልተካከለ ዳግም›› ይባላል፡፡ ፍጹም የሆነ መመሳሰል የሌለው መደገም እንደማለት ነው፡፡ ዳግም ምጽአት፣ ዳግም ልደት፣ ዳግም ትንሣኤ ወዘተ ‹‹ያልተካከለ ዳግም››......
Read More