Start Blog Type 1 (Full Width Image) and Sidbar

04
Aug 2020
የልጆችና የወላጆች ልዩ መርሐ ግብር ተካሄደ

በሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን የተጋጀው ልዩ የልጆችና የወላጆች መርሐ ግብር ለመጀመሪያ ጊዜ ተካሄደ! በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በስዊድንና ስካንዲናቪያን ሀገሮች ሀገረ ስብከት በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በጽጌ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው ልዩ የልጆችና የወላጆች መርሐ ግብር ቅዳሜ ሐምሌ 25/11/2012 በሰሜናዊ ሄልስንኪ በተለምዶ ሃጋ አካባቢ በሚገኘው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ ተከናውኗል። በአይነቱ ልዩ የሆነው የልጆች እና የወላጆች መርሐ ግብርን በጸሎትና ያስጀመሩት የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ አሚን ቀሲስ ለማ በሱፍቃድ ነበሩ። በመቀጠልም መርሐ ግብሩን ያዘጋጁት በጽጌ......

Read More


26
Apr 2020
ቤተ ክርስቲያኗ ልጆቿ ምእመናን  ያሉበትን ሁኔታ የሚከታተል ኮሚቴ ማዋቀሯ ተገለጠ

በስዊድንና እስካንድናቪያን ሀገሮች ሀገረ ስብከት በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ዓለምን እያስጨነቀ የሚገኘው በኮረና ቫይረስ እየቀጠፈ ያለው ሕዝብ በዝርወት ከሚከኙት መካከል ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያ ተጠቃሾች መሆናቸው የሚታወቅ በመሆኑ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት በሥሯ አገልግሎት የሚያገኙትን በመላዋ ፊንላንድ የሚገኙትን ምእመናንን ጤንነት እና አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ የመረዳዳት በጎ ተግባር የሚያስተባብር ኮሚቴ ማዋቀሯን የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ አሚን ለማ በሱፍቃድ ገለጹ፡፡ ኮሚቴው የአጥቢያው ምእመናን በዚህ ቫይረስ ቢያዙ እንኳን አስፈላጊውን ማኅበራዊ ሥነ ልቡናዊና ተመሳሳይ እገዛዎችን ለማድረግ እንደሚያስተባብር ተጠቁሟል ፡፡ ኮሚቴው ከሄልሲንኪ ውጪ ባሉት ምእመናን ባሉባቸው ከተሞችም የመረዳዳት አገልግሎቱን ተደራሽ የሚያደርግበትን አቅጣጫም ማስቀመጡን ታውቋል፡፡......

Read More


21
Jan 2020
በፊንላንድ ሄልሲንኪ የጥምቀት በዓል  በታላቅ  ድምቀት ተከበረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በየዓመቱ ጥር  11 /አሥራ አንድ የሚከበረው የጌታችን የአምላካችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በሄልሲንኪ ደብረ አሚን ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን  በተለየ  ሃይማኖታዊ ድምቀት ተከብሯል። የጥምቀት በዓል በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባሕል ድርጅት (ዩኔስኮ) መመዝገቡን ተከትሎ  ዘንድሮ  ሥርዓቱን በጠበቀና በደመቀ  መልኩ   ታቦተ ሕጉ በምእመናን ታጅቦ ከበዓሉ ዋዜማ  በሚከበረው የከተራ በዓል ጊዜያዊ ማረፊያው ጉዞ አድርጎል:: ከዋዜማው ጀምሮ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ድምቀት የተጀመረው የጥምቀት በዓሉ ሌሊቱን በካህናቱ አገልግሎት አድሮ ከሌሊቱ 10 /አሥር ሰዓት/ ጀምሮ የቅዳሴ ሥነ ሥርዓቱ ቀጥሏል። የቅዳሴው ሥርዓት ከተፈፀመ በኋላ ባሕረ ጥምቀቱ ተባርኮ ሕዝበ ክርስቲያኑም ጠበል ተረጭቷል። የደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ  ቀሲስ......

Read More


29
Aug 2019
በዓለ እረፍቱ ለአቡነ ተክለሃይማኖት በደማቅ ሥነ ሥርዓት ተከበረ

በስዊድንና እካንድናቪያን ሀገሮች ሀገረ ስብከት በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በዓለ እረፍቱ ለአቡነ ተክለሃይማኖት ነሐሴ 18 እና 19/2011 ዓ.ም በድማቅ ሥነ ሥርዓት ተከበረ። በበዓሉ ላይ የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የተገኙ ሲሆን ሌሎችም ከ አውሮጳ ከተለያዩ አድባራት የተጋበዙ ሊቃውንትም በበዓሉ ተገኝተዋል ። ብፁዕ አቡነ ኤልያስ ከበዓሉ ቀደም ብለው ሄልሲንኪ የገቡ ሲሆን ከፊንላንድ ኦርቶዶክስ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሊዮ ጋር የፊንላንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርትሲያን ለቤተ ክርስቲያናችን እስካሁን ላደረገችውና እያደረገች ላለው ትብብር አመስግነዋል። ወደፊትም ለአስፈላጊው አገልግሎት ሁሉ እንዲተባበሩ ጥሪ ከማቅረባቸው በተጨማሪም የጋራ በሆኑ አገልግሎቶች ተባብሮ መሥራትን በተመለከተ በማንሳት ውይይት አድርገዋል ።......

Read More


Social Icons

Calendar

April 2024
M T W T F S S
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
2930  

instagram

    flickr

    instagram