Start Blog Type 1 (Full Width Image) and Sidbar

25
Jul 2021
የአገልግሎት ምስጋና መርሐ ግብር ተዘጋጀ

በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ለወ/ሮ አለማች ገብረ ሚካኤል የአገልግሎት የምስጋና ምስክር ወረቀት ተሰጠ። በሀገረ ፊንላንድ ከሦስት ዐሥርት ዓመታት በላይ በመንፈሳዊ አገልግሎት በማኅበራዊ አገልግሎት ለሚታውቁት ወ/ሮ አለማች ፣ ሐምሌ ፲፯/፳፻፲፫ ዓ.ም በሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን የአገልግሎት የምስጋና መርሐ ግብር ተዘጋጀ ። በዕለቱም በመርሐግብሩ የታደሙት ምእመናን ወ/ሮ አለማች በሀገረ ፊንላንድ በስደት ለሚገኙት ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያ ያዘነውን በማጽናናት ፣ በመጠየቅ የሀገረ ፊንላንድንም ሥርዓተ ሀገሩንም በማለማመድ ከፍተኛ አገልግሎት ማበርከታቸውን ተናግረዋል ። ወ/ሮ አለማች በተለይ በመንፈሳዊ ሕይወታቸው ከታላቁ ካህን አባታቸውና ከለጋሷ እናታቸው የወረሱትን በጎ ተግባር ስደቱ ተጽእኖ ሳይፈጥርባቸው ሃይማኖታዊ ሥርዓታቸውን......

Read More


26
Dec 2020

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በስዊድንና ስካንድኔቪያን ሀገሮች ሀገረ ስብከት በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ቤተክርስቲያን እሑድ ታኅሣሥ 11 ቀን /2013 (20.12.2020) በርቀት በስካይፔ ባካሄደው ዓመታዊ የአጥቢያ ምእመናን መንፈሳዊ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በፈረንጆቹ ከ2021 ዓ.ም ጀምሮ በደብሩ የውስጥ መተዳደሪያ ደንብ መሠረት ለቀጣይ ሁለት ዓመታት ቤተክርስቲያኗን የሚያገለግሉ አዲስ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ አባላ ምርጫን አካሄዷል። ጠቅላላ ጉባኤውን በጸሎት ክፍተው የመሩት የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ አሚን ቀሲስ ለማ በሱፍቃድ የዕለቱን አጀንዳዎች ማለትም  የደብሩን የውስጥ መተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ ነጥቦች ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ  የ2021 በጀት ዓመት ማጽደቅ  የሰበካ ጉባኤ ምርጫ ማከናወን መሆናቸውን ገልጠዋል ። የጠቅላላ ጉባኤ የምርጫው......

Read More


14
Sep 2020
የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በዓለ እረፍት በደማቅ ሥነ ሥርዓት በሄልሲንኪ ተከበረ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በስዊድንና ስካንድኔቪያን ሀገሮች ሀገረ ስብከት በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን የጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት በዓለ እረፍት ክብረ በዓል ነሐሴ 24 ቀን 2012 ዓ.ም. ተከበረ። በበዓሉ ላይ የኢትዮጵያና የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ካህናት፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እና ምእመናን ተገኝተዋል። በዓሉ ቅዳሜ ነሐሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም ምሽት የጻድቁን ገድል በመተርጎም የተጀመረ ሲሆን፤ ከመንፈቀ ሌሊት ጀምሮ ማኅሌት ተቋሟል። ከማኅሌቱ በመቀጠል እሑድ ጠዋት የቅዳሴ ጸሎት ከተከናወነ በኋላ በዓሉ አስመልክቶ በደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ አሚን ቀሲስ ለማ በሱፈቃድ ትምህርት ተስጥቷል። በትምህረቱም ላይ የደብሩ አስተዳዳሪ ባስተላለፉት መልእክት የጻድቁ አቡነ ተክለ......

Read More


26
Aug 2020

 በፊላንድ ታምፔሬ ከተማ ለመጀመሪያ ጊዜ ሥርዓተ ቅዳሴ ተከናወነ። የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ኪዳነ ምሕረት የጽዋዕ ማኅበር ጥቅምት 1/2012 ዓ ም የተቋቋመ ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ቅዳሜ ነሐሴ 16 ቀን 2012 ዓ.ም ( 22/8/2020 ) Tuomiokirkokatu 27 ላይ በሚገኘው የፊላንድ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የቅዳሴው አገልግሎት የተመራው  በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በስዊድንና ስካንዲናቪያን ሀገሮች ሀገረ ስብከት የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ አሚን ቀሲስ ለማ በሱፍቃድ እንዲሁም በፊላንድ የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ደብረ ሰላም መድኅንያዓለም ቤተክርስቲያን ምክትል አስተዳዳሪ  ቀሲስ አንገሶም  ዲያቆናት አማካኝነት የተፈጸመ ሲሆን የሄልሲንኪ ደብረ አሚን ጽጌ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት መዘምራን እንዲሁም ከፊላንድ ከተለያየ......

Read More


Social Icons

Calendar

April 2024
M T W T F S S
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
2930  

instagram

    flickr

    instagram