ዳግም ትንሣኤ (ለሕፃናት)
![ዳግም ትንሣኤ (ለሕፃናት)](http://www.teklehaymanot.fi/wp-content/uploads/2016/05/ዳግመ-ትንሣኤ.png)
by ግንኙነት ክፍል
ጌታችን በተነሣበት ዕለት የክርስቶስ ደቀመዛሙርት ተሰብስበው ሳለ ጌታችን በመካከላቸው ቆመና “ሰላም ለእናንተ ይሁን “አላቸው፡፡ የነበሩበት ቤት በሩም መስኮቱም ተቆልፎ ስለነበር ደቀ መዛሙርቱም በጣም ደነገጡ፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም “አትፍሩ እኔ አምላካችሁ ነኝ” ብሎ የተወጋ ጎኑን እና የተቸነከሩ እጆቹን አሳያቸው፡፡ እነርሱም ጌታ ከሞት መነሣቱን አመኑ፡፡ ደቀመዛሙርቱንም(ተማሪዎቹንም) ሕዝቡን እንዲያስተምሩ ላካቸው፡፡
በዚህ ዕለት ከ12ቱ ደቀመዛሙርት አንዱ የሆነው ቶማስ ከእነርሱ ጋር አልነበረም፡፡ ደቀመዛሙርቱ የጌታን መነሣት እና እነርሱም እነዳዩት ነገሩት፡፡ እርሱ ግን በዓይኔ ካላየሁ አላምንም አለ፡፡
ከስምነት ቀን በኃላ እንደገና ቶማስ አብሯቸው ሳለ በሩ እንደተዘጋ ጌታችን መጣ፣ በመካከላቸውም ቆሞ “ሰላም ለእናንተ ይሁን” አላቸው፡፡ ቶማስ ትንሣኤውን እነደተጠራጠረ ስላወቀ እጅህን አምጣና የተወጋ ጎኔን እና የተቸነከሩ እጆቼን ዳስስ አለው፡፡ ቶማስም በዳሰሰው ጊዜ አምላክ መሆኑን ዐወቀ፡፡ ይኽ ዕለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሁለተኛ ጊዜ ቶማስ ባለበት ለደቀመዛሙርቱ የተገለጠበት ዕለት በመሆኑ ዳግም ትንሣኤ ተብሎ ተሰየመ፡፡ ዳግም ማለት ሁለተኛ ማለት ነው እሽ ልጆች፡፡
በእኅተ ፍሬስብሐት
source http://eotcmk.org
Recommended Posts
![ስለ አቤልና ቃየን (ለሕፃናት)](http://www.teklehaymanot.fi/wp-content/uploads/2017/12/አቤል-እና-ቃዬል-4-420x330.jpeg)
ስለ አቤልና ቃየን (ለሕፃናት)
December 27, 2017
![ስለ እመቤታችን ልደት (ለሕፃናትና ዠማሪዎች)](http://www.teklehaymanot.fi/wp-content/uploads/2017/12/የእመቤታችን-ልደት-420x330.jpg)
ስለ እመቤታችን ልደት (ለሕፃናትና ዠማሪዎች)
December 26, 2017
![ልደተ ክርስቶስ /የገና በዓል/ - ለሕጻናት](http://www.teklehaymanot.fi/wp-content/uploads/2017/01/Birth-of-Jesus-The-Federalist-Papers-420x330.jpg)
ልደተ ክርስቶስ /የገና በዓል/ – ለሕጻናት
January 07, 2017