NewsTicker


27
Jul 2018

ሲኖዶሳዊው የዕርቀ ሰላም ልኡካን አባቶች ስምምነት ዝርዝር: ኹለቱም ቅዱሳን ፓትርያርኮች በእኩል የአባትነት ክብር ያገለግላሉ   አንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን፣ በአንድ የቅዱስ ሲኖዶስ አመራር ትመራለች፤ 4ኛው ፓትርያርክ በጸሎት እና በቡራኬ፣ 6ኛው ፓትርያርክ በአስተዳደር ሥራ፤ የኹለቱም ስም፣ቤተ ክርስቲያን ባለችበት ዓለም ሁሉ ዘወትር በጸሎት ይነሣል፤ ሰማዕቱ አቡነ ቴዎፍሎስ ለሞት ከተላለፉበት ጀምሮ የቀኖና ጥሰት ተፈጽሟል፤ ቅ/ሲኖዶስ፣ የቤተ ክርስቲያንን ክብር ባለማስጠበቁ ልጆቿን ይቅርታ ይጠይቃል፤ ††† ጥሰቱን ለመከላከልና ሉዓላዊነቷን ለማስጠበቅ፣ቅዱስ ሲኖዶስ ደንብ ያዘጋጃል፤ በኹለቱም ሲኖዶስ የተላለፈው ቃለ ውግዘት፣ በጋራ ምልዓተ ጉባኤ ይፈታል፤ ከልዩነት በኋላ የተሾሙ ቅቡል ናቸው፤አጠራራቸው እንደ ቅደመ ተከተላቸው፤ ለውጭ ቤተ ክርስቲያን፣የየሀገሩን ሕገ መንግሥት ያገናዘበ መመሪያ ይወጣል፤ የስምምነቱን ተግባራዊነትና......

Read More


05
Jul 2018

የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤ/ክ በሁለቱ ሲኖዶሶች መሓከል የተጀመረውን እርቀ ሰላም እንደሚደግፍ አስታወቀ፡፡ እርቀ ሰላሙን በሚመለከት በወጣው ባለ አምስት ነጥብ የአቋም መግለጫ ላይ እንደተጠቆመው የሁለቱ ሲኖዶሶች አባቶች እርቀ ሰላሙን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈጽሙ፣ ለእዚህም ሂደት የተቋቋመው አስተባባሪ ኮሚቴ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ደብሩ እንደሚደግፍ ተጠቁሟል፡፡ በተጨማሪም፣ በአጥቢያው እና በውጭ አባቶች አስተዳደር ሥር ያሉ ማኅበረ ምእመናን እንዲሁም ሌሎች ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያን የእርቀ ሰላሙን ሂደት እንዲደግፉ እና ለእርቁ መሳካትም አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ተላልፏል፡፡  ...

Read More


25
May 2018
ሰባተኛ ዓመት ምሥረታና ፍልሰተ ዐፅሙ ለአቡነ ተክለሃይማኖት በዓል በደማቅ ሁኔታ ተከበረ

ሰባተኛ ዓመት ምሥረታና ፍልሰተ ዐፅሙ ለአቡነ ተክለሃይማኖት በዓል በደማቅ ሁኔታ ተከበረ በየዓመቱ በታላቅ ድምቀት የሚከበረው ፍልሰተ ዐፅሙ ለአቡነ ተክለሃይማኖት ዓመታዊ ክብረ በዓል እና የደብሩ ሰባተኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በዘንድሮ ዓመት በተለየ ሁኔታ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ በፊንላንድ  የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን ቅዳሜ ግንቦት 11 2010 ዓ.ም ተከብሮ ዋለ :: በዕለቱ ታቦተ አቡነ ተክለሃይማኖት ወደ ፊንላንድ የመጣበት እና ደብሩ እንደ አጥቢያ ቤተክርስቲያን  የተመሠረተበት ሰባተኛ ዓመት “ ሃይማኖታችንን ለልጆቻችን ዛሬ እናስተምር” በሚል መሪ ቃል በፊንላንድ ሄልሲንኪ የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ ሊቀ ማእምራን ቀሲስ ዮሴፍ ምክትል አስተዳዳሪ መልአከ ሰላም ቀሲስ ......

Read More


13
Feb 2018
ልዩ የሕጻናትና አዳጊዎች መርሐ ግብር ተካሄደ

“ልጆቻችሁንም አስተምሩአቸው፥ በቤትህም ስትቀመጥ፥ በመንገድም ስትሄድ፥ ስትተኛም ስትነሣም አጫውቱአቸው” ዘዳ. ፲፩፥፲፱ የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ መመሪያ ምክንያት በማድረግ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አውሮጳ ሀገረ ስብከት በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤት ክፍል የሕፃናትና አዳጊዎች ንዑስ ክፍል አዘጋጅነት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደትና የጥምቀት በዓልን ምክንያት በማድረግ እሑድ ጥር 20 ቀን 2010 ዓ.ም. (January 28, 2018) ከሰዓት በኋላ ልዩ የሕጻናት እና የአዳጊ ልጆች መርሐ ግብር ተካሄደ።   በመርሐ ግብሩ መጀመሪያ ላይ ከሰንበት ትምህርት ቤት ክፍል በተላለፈው መልእክት ሕፃናትና አዳጊዎች ልጆች የነገ የቤተ ክርስቲያናችን ተረካቢዎች በመሆናቸው ለእነርሱ......

Read More


16
Jan 2018
የ2018 ጠቅላላ መንፈሳዊ ጉባኤ ተካሄደ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰሜን ምዕራብ አውሮፖ ሀገረ ስብከት በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን የአጥቢያው ምእመናን በተገኙበት እሑድ ጥር 6 2010ዓ.ም. ወይም Jan 14.2018 በፑኪንማኪ የመሰባሰቢያ አዳራሽ እ.ኤ.አ. የ2018 ጠቅላላ መንፈሳዊ ጉባዔ ተካሄደ፡፡ በጉባኤው መጀመሪያ ላይ የ2017 የክፍሎች የዕቅድ አፈጻጸም እና፣  የሒሳብ ሪፖርት እንዲሁም  የኦዲት ምርመራ ሪፖርቶች ለጉባኤው ቀርበዋል፡፡  ሪፖርቶቹ ከቀረቡ በኋላ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎች እና አስተያየቶች የተሰጡ ሲሆን ለቀረቡ ጥያቄዎችም ከክፍል ተወካዮች እና ከደብሩ አስተዳዳሪ ምላሽ ተሰጥቶ ጉባኤው ሪፖርቶቹን አጽድቋል፡፡ በመቀጠልም እ.ኤ.አ. የ2018 በጀት ዓመት የክፍሎች ዕቅድ ለጉባኤው የቀረበ ሲሆን የቀረበውን ዕቅድ ተከትሎም ከተሳታፊዎች አስተያየት እና ማሳሰቢያ የተሰጠ ሲሆን በተለይ......

Read More


26
Dec 2017
የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በቫሳ ከተማ ተከበረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የቤተክርስቲያን ሰሜን ምዕራብ አውሮፖ ሀገረ ስብከት በፊንላንድ ቫሳ ከተማ የሚኖሩ ምእመናን ባቋቋሙት የቅዱስ ገብርኤል ጽዋዕ ማኅበር አስተባባሪነት ዓመታዊው የቅዱስ ገብርኤል በዓል ባሳለፍነው ቅዳሜ ታኅሣሥ 14 ቀን 2010 ዓ.ም በሥርዓተ ቅዳሴና በጉባኤ ተከብሮ ውሏል። በሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን የሚያገለግሉ ካህናት፤ እንዲሁም ከደብሩ መዘምራን የተወሰኑት ለዚሁ አገልግሎት ከአርብ ጃምሮ በቦታው በመድረስ ቫሳ በሚገኘው የፊንላንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ለምእመናኑ ቅዳሴ ትምህርትና ምክር አገልግሎት ተሰጥቷል። በተለይም ከቅዳሴው በኋላ በተካሄደው ጉባኤ ላይ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ቀሲስ ለማ በሱፈቃድ በዓሉን የተመለከተና ከምእመናን ሕይወት ጋር በማያያዝ ሰፋ......

Read More


23
Nov 2017
የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል በድምቀት ተከበረ

በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ዘንድ በየዓመቱ ሕዳር 12 ቀን የሚከበረው የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል ከትላንት በስትያ ከሄልሲንኪ ከተማ ተጉዘው በቦታው በተገኙ ኢትዮጵያውናን እና ኤርትራውናን ሕዳር 9 ቀን 2010 ዓ.ም በፊላንድ በድምቀት  ተክብሯል። ከፊላንድ ዋና ከተማ ሄልሲንኪ 150 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው በቱርኩ ከተማ በሰማዕቱ በቅዱስ አሌክሳንደር የፊላንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ከማላዳው  ጀምሮ በቅዳሴ  የተጀመረው የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል ቀኑን ሙሉ የተለያዩ መንፈሳዊ መዝሙሮች እና ትምህርቶች ቀርበውበታል ። በፊላንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ቀሲስ ለማ በሱፍቃድ የወንጌል ትምህርት ሰጥተዋል።የደብረ አሚን አቡነ......

Read More


29
Sep 2017
የመስቀል ደመራ በዓል ለሁለተኛ ጊዜ በሄልሲንኪ ተከበረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በፊንላንድ ሄልሲንኪደብረ አሚን አቡነተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በሄልሲንኪ ከተማ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን አደባባይ የመስቀል ደመራ በዓል ለሁለተኛ ጊዜ ተከበረ። ከባለፈው ዓመት በተለየ መልኩ የደመራ አዘጋጅ ኮሚቴ ተመርጦ ከፍተኛ ዝግጅት ተደርጎ መስከረም 16 ቀን 2010 ዓ.ም. ከ 17፡30 – 20፡30 በተካሄደው የደመራ ሥነ ሥርዓት ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ በፊንላንድ የሚገኙ የኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ምእመናን እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የልዩ ልዩ ቤተ እምነት መሪዎች ፡ የመንግሥት እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ሓላፊዎችና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በበዓሉ ተገኝተዋል፡፡ በደብሩ ካህናትና ዲያቆናት መሪነት ዕለቱን የሚያዘክር ስብሐተ እግዚአብሔር ከደረሰ  በኋላም በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በዓሉን የሚመለከት ወረብ ቀርቧል፡፡......

Read More


22
May 2016
በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ደብር የአንድ ቀን ዐውደ ርእይ ተካሄደ

በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ደብር ግንቦት 13/2008 ዓ.ም (May 21 2016) “የእናት ቤተ ክርስቲያናችንን አደራ እንጠብቅ አንድነታችንንም አንተው” በሚል መሪ ቃል ልዩ የአንድ ቀን ዐውደ ርእይ ተካሄደ። ዐውደ ርእዩን መርቀው የከፈቱት የፊኒሽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የተለያዩ ባህል ተጠሪ ቄስ ቴሙ ቶኦይቪነን ፣ ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ አንተነህ ጉደታ በኦስሎ ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም አስተዳዳሪ ፣ የደብሩ አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ለማ በሱፍቃድ ነበሩ ። እንዲሁም ቄስ ሚካኤል ሰንድቪስት ከቲኩሪላ ፊኒሽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን፣ ሚስተር ቬሪኮቨ ሌፍ የሄልሲንኪ ከተማ አስተዳደር የአስተዳደር ክፍል የበላይ ሃላፊ፣ አቶ ኤልያስ ሳቦሬ በፊንላንድ የኢትዮጲያ ኮንስላር በክብር እንግድነተ ተገኝተዋል ።......

Read More


22
Apr 2016
በሄልሲንኪ ከተማ አውደ ርዕይ ሊካሄድ ነው

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን “የእናት ቤተ ክርስቲያናችንን አደራ እንጠብቅ አንድነታችንንም አንተው” በሚል መሪ ቃል ልዩ የአውደ ርዕይ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሚያካሄድ አስታወቀ። ግንቦት 12 2008 ዓም በሄልሲንኪ ከተማ ይካሄዳል የተባለው መርሐ ግብር አላማው  የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ዕውቅና እንዲኖረው ማድረግ። ወደፊት ስለ ተረካቢ ህፃናትና ከፊንላንድ መንግስትና ለሚመለከታቸው ግንዛቤ መፍጠር በፊንላንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አመሰራረት ታሪክና ዛሬ ያለንበትን ደረጃ ማስተዋወቅ ናቸው። በዝግጅቱ ላይ ከተለያዩ ቤተ እምነቶች ከመንግስትና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች እንግዶች ይጋበዛሉ።አውደ ርዕዩ ከቤተ ክርስቲያኗ 5ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ጋር በጋራ ይከበራል።...

Read More