18
Aug 2016
በቫሳና አካባቢው ለሚኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች እሑድ ነሐሴ 8 2008 ዓ.ም. ከሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ወደ ስፍራው በተጓዙ አገልጋዮች አማካኝነት ለመጀመሪያ ጊዜ የቅዳሴና የሥርዓተ ጥምቀት አገልግሎት ተከናውኗል፡፡ በዕለቱ በተካሄደው መንፈሳዊ አገልግሎት በአካባቢው የሚገኙ የእምነቱ ተከታዮች የተሳተፉ ሲሆን ለሰባት ሕጻናትም ሥርዓተ ጥምቀት ተፈፅሟል፡፡ ቫሳ ውስጥ መንፈሳዊ አገልግሎት በመደበኛ የሰንበት ጉባኤ አማካኘነት ላለፉት አራት ዓመታት ይሰጥ እንደነበርና፣ የቅዳሴ አገልግሎት ለማግኘት ግን ሕዝበ ክርስቲያኑ ወደ ሄልሲንኪ በመጓዝ ወይም በሁለት ወር አንድ ጊዜ በግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በሚዘጋጅ መንፈሳዊ አገልግሎት ይሳተፍ እንደነበር በአገልግሎቱ ላይ የተገኙ ምእመን ገልጸዋል፡፡ በአግልግሎቱ ላይ የተሳተፉ የአካባቢው ነዋሪዎች......
Read More