Daily Archives: July 30, 2018


30
Jul 2018

የተላኩብፁዓን አባቶች፣የተደረሰበትን ስምምነት የሚያስረዳ መግለጫ ለጉባኤው አቀረቡ፤ የነበረው የአባቶች መለያየት ለውግዘት በሚዳርግ ደረጃ ላይ ደርሶ እንደነበር የታወቀ ነው፤ የተደከመበት ዕርቀ ሰላም ለውጤት በመብቃቱ በስምምነቱ መሠረት ውግዘቱ ተነሥቶአል፤ የጳጉሜ 1984፣ የመስከረም 1985፣ የጥር 1999ዓ.ም.ቃለ ውግዘት፣ከዛሬ ጀምሮ ተነሥቶአል፤ ከልዩነት በፊት የተሾሙ ነባር ሊቃነ ጳጳሳትንና ከልዩነት በኋላ የተሾሙትን ተቀብሏቸዋል፤ ††† ስያሜያቸው እንዳለ እንደተጠበቀ፣በውጭ ሀገርም ኾነ በሀገር ቤት ተመድበው ያገለግላሉ፤ ከ1-6 ተራቁጥር የተዘረዘሩትን የዕርቀ ሰላም ነጥቦች ምልዓተ ጉባኤው ተቀብሎ አጽድቋል፤ የቤተ ክርስቲያናችን አንድነትና የሀገር ሰላም የበለጠ እንዲጠናከር የበኩሉን ይፈጽማል፤ ጠ/ሚሩ፣ ችግሩ የሀገርም መኾኑን በመገንዘብ አስተጋባኢና አሰባሳቢ መመሪያ ሰጥተዋል፤ ብዙ የተደከመበት ጉዳይ ፈጣን መፍትሔ እንዲያገኝ ስላደረጉ ልባዊ ምስጋና ያቀርባል:: ††† ምንጭ: ሐራ ዘተዋሕዶ...

Read More