20
Jun 2017
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዘንድ በየዓመቱ ሰኔ 12 ቀን የሚከበረው ዓመታዊው የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል በቱርኩ- ፊላንድ ሰኔ 10/2009 ዓ .ም በደመቀ ሁኔታ ተከበረ። በዘንድሮ ዓመት ከሌላው ጊዜ በተለየ መልኩ በርካታ ምእመናን ወደ ቱርኩ ተጉዘው በዓሉን ያከበሩ ሲሆን ፣ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ መልኩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሐዶ እና የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አቢያተ ክርስቲያናት ካህናት እና ምእመናን በጋራ በተገኙበት በማኅሌትና በቅዳሴ ከማለዳው የተጀመረው ክብረ በዓል ቀኑን ሙሉ ቀጥሎ ከቅዳሴው ፍፃሜ በኋላም ትምህርትና እና ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ዝግጅቶች ቀርበዋል ። በፊላንድ ሄልሲንኪ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ቀሲስ......
Read More