የእርቀ ሰላሙን ሂደት የሚደግፍ የአቋም መግለጫ ወጣ

የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤ/ክ በሁለቱ ሲኖዶሶች መሓከል የተጀመረውን እርቀ ሰላም እንደሚደግፍ አስታወቀ፡፡ እርቀ ሰላሙን በሚመለከት በወጣው ባለ አምስት ነጥብ የአቋም መግለጫ ላይ እንደተጠቆመው የሁለቱ ሲኖዶሶች አባቶች እርቀ ሰላሙን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈጽሙ፣ ለእዚህም ሂደት የተቋቋመው አስተባባሪ ኮሚቴ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ደብሩ እንደሚደግፍ ተጠቁሟል፡፡ በተጨማሪም፣ በአጥቢያው እና በውጭ አባቶች አስተዳደር ሥር ያሉ ማኅበረ ምእመናን እንዲሁም ሌሎች ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያን የእርቀ ሰላሙን ሂደት እንዲደግፉ እና ለእርቁ መሳካትም አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ተላልፏል፡፡
Recommended Posts

ማኅሌተ ጽጌ ወደ ፊንላንድኛ ቋንቋ ተተርጉሞ ተመረቀ
October 04, 2023

ሀገረ ስብከቱ የ2015 በጀት ዓመት አፈጻጸም ጠቅላላ ጉባኤውን አጠናቀቀ
September 03, 2023

በፊንላንድ ሀገር የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት አዲስ ሕንጻ ቤተክርስቲያን ቡራኬ ተከናወነ !
September 03, 2023