በዓለ ጥምቀት በደማቅ ሁኔታ ተከበረ

by ግንኙነት ክፍል
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አውሮጳ ሀገረ ስብከት በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ጥር 13 ቀን የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት ቲኩሪላ በሚገኘው በፊኒሽ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በደማቅ ሁኔታ ተከበረ።
በዕለቱ በተያዘው መርሃ ግብር መሠረት ሥርዓተ ቅዳሴው ከተከናወነ በኋላ የባህረ ጥምቀቱ ሥርዓተ ጸሎት ተደርሶ ህዝቡም ጸበል ተረጭቶ የበረከቱ ተካፋይ ሆኗል፡፡በመቀጠልም በደብሩ መዘምራን ዕለቱን የተመለከተ ያሬዳዊ ዜማ የቀረበ ሲሆን በመጨረሻም በደብሩ አስተዳዳሪ በመጋቤ ብሉይ ቀሲስ ለማ በሱፈቃድ ትምህርተ ወንጌል እና ጸሎተ ቡራኬ ከተሰጠ በኋላ የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል።
ጥምቀት በዓል አከባበር 2009
Recommended Posts

ማኅሌተ ጽጌ ወደ ፊንላንድኛ ቋንቋ ተተርጉሞ ተመረቀ
October 04, 2023

ሀገረ ስብከቱ የ2015 በጀት ዓመት አፈጻጸም ጠቅላላ ጉባኤውን አጠናቀቀ
September 03, 2023

በፊንላንድ ሀገር የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት አዲስ ሕንጻ ቤተክርስቲያን ቡራኬ ተከናወነ !
September 03, 2023