በቫሳ ለመጀመሪያ ጊዜ የቅዳሴና የሥርዐተ ጥምቀት አገልግሎት ተሰጠ

በቫሳ ለመጀመሪያ ጊዜ የቅዳሴና የሥርዐተ ጥምቀት አገልግሎት ተሰጠ

በቫሳና አካባቢው ለሚኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች እሑድ ነሐሴ 8 2008 ዓ.ም. ከሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ወደ ስፍራው በተጓዙ አገልጋዮች አማካኝነት ለመጀመሪያ ጊዜ የቅዳሴና የሥርዓተ ጥምቀት አገልግሎት ተከናውኗል፡፡ በዕለቱ በተካሄደው  መንፈሳዊ አገልግሎት በአካባቢው የሚገኙ የእምነቱ ተከታዮች የተሳተፉ ሲሆን ለሰባት ሕጻናትም  ሥርዓተ ጥምቀት ተፈፅሟል፡፡

ቫሳ ውስጥ መንፈሳዊ አገልግሎት በመደበኛ የሰንበት ጉባኤ አማካኘነት ላለፉት አራት ዓመታት ይሰጥ እንደነበርና፣ የቅዳሴ አገልግሎት ለማግኘት ግን ሕዝበ ክርስቲያኑ ወደ ሄልሲንኪ በመጓዝ  ወይም በሁለት ወር አንድ ጊዜ  በግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በሚዘጋጅ መንፈሳዊ አገልግሎት ይሳተፍ እንደነበር በአገልግሎቱ ላይ የተገኙ ምእመን ገልጸዋል፡፡

በአግልግሎቱ ላይ የተሳተፉ የአካባቢው ነዋሪዎች በሰጡት አስተያየት ከዚህ ቀደም በተለይ ሕጻናትን ክርስትና ለማስነሳት ሁኔታዎች የተመቻቹviber image12 እንዳልነበሩ በማስታወስ በከተማቸው ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችን አገልጋዮች  አማካኝነት በተሰጠው የቅዳሴና ትምህርት  አገልግሎት መደሰታቸውን ገልፀው ፣ አገልግሎቱ ቀጣይነት እንዲኖረውም አያይዘው ጠይቀዋል፡፡

የተጀመረውን አገልግሎት ለማስቀጠል ይረዳ ዘንድ በዕለቱ ሦስት ምእመናን ያሉበት አስተባባሪ ኮሜቴ የተመረጠ ሲሆን፣ ሕዝበ ክርስቲያኑን በማስተባበር፣ ለአገልግሎት የሚሆን ቦታ በማስፈቀድና በአጠቃላይ አገልግሎቱ የሚቀጥልበትን ሁኔታዎች ለማመቻቸት እንደሚሰራ ታውቋል፡፡

ለመንፈሳዊ አገልግሎቱ ከሄልሲንኪ ወደ ቫሳ ተጉዘው የነበሩት የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ቀሲስ ለማ በሱፈቃድ ስለ ሁኔታው በሰጡት አስተያየት፣ በቫሳ በነበረው መንፈሳዊ አገልግሎት ላይ ሕዝቡ ያሳየውን ተሳትፎና በቫሳ የፊኒሽ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ያደረገውን ትብብር  አድንቀው ፣  በከተማው የተመሠረተው የቅዱስ ገብርኤል ጽዋ ማኅበር፣  በዓመታዊ የቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓላት ላይ የቅዳሴ መርሃ ግብር ያዘጋጅ ዘንድ የአካባቢውን ሕዝበ ክርስቲያን ማሕበሩን ማጠናከር እንደሚገባው ገልጸዋል፡፡  አያይዘውም በሄልሲንኪ የሚኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት አጥቢያ ምእመናን እንደ ከዚህ ቀደሙ ማኅበራትን በማጠናከር ረገድ የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል፡፡

አስተዳዳሪው አክለው እንደገለጹት፣ በቀጣይነትም በርከት ያሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባላት በሚኖሩባቸው ትላልቅ  የፊንላንድ ከተሞች ተመሳሳይ መንፈሳዊ አገልግሎት ለመስጠት መታሰቡና በጽዋ ማኅበርነት በማደራጀት ወደ ፊት ራሳቸውን ችለው ወደ ቤተ ክርስቲያንነት የሚያድጉበትን ሁኔታ የማመቻቸት ሥራ ለመሥራት መታሰቡን ገልጸዋል፡፡

ከሄልሲንኪ ውጪ በቱርኩ የቅዱስ ሚካኤል ጽዋ ማኅበር እንዳለና በዓመት ሁለት ጊዜ የቅዱስ ሚካኤልን ዓመታዊ ክብረ በዓላትን ምክንያት በማድረግ የቅዳሴና የትምህርተ ወንጌል አገልግሎት እንደሚያዘጋጅ ይታወቃል፡፡viber image7

share

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *