በሄልሲንኪ ከተማ አውደ ርዕይ ሊካሄድ ነው
![በሄልሲንኪ ከተማ አውደ ርዕይ ሊካሄድ ነው](http://www.teklehaymanot.fi/wp-content/uploads/2015/05/ልዪ-ዐውደ-ርአይ.jpg)
by ግንኙነት ክፍል
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን “የእናት ቤተ ክርስቲያናችንን አደራ እንጠብቅ አንድነታችንንም አንተው” በሚል መሪ ቃል ልዩ የአውደ ርዕይ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሚያካሄድ አስታወቀ። ግንቦት 12 2008 ዓም በሄልሲንኪ ከተማ ይካሄዳል የተባለው መርሐ ግብር አላማው የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ዕውቅና እንዲኖረው ማድረግ። ወደፊት ስለ ተረካቢ ህፃናትና ከፊንላንድ መንግስትና ለሚመለከታቸው ግንዛቤ መፍጠር በፊንላንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አመሰራረት ታሪክና ዛሬ ያለንበትን ደረጃ ማስተዋወቅ ናቸው። በዝግጅቱ ላይ ከተለያዩ ቤተ እምነቶች ከመንግስትና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች እንግዶች ይጋበዛሉ።አውደ ርዕዩ ከቤተ ክርስቲያኗ 5ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ጋር በጋራ ይከበራል።
Recommended Posts
![ማኅሌተ ጽጌ ወደ ፊንላንድኛ ቋንቋ ተተርጉሞ ተመረቀ](http://www.teklehaymanot.fi/wp-content/uploads/2023/10/DSC_5690-scaled.jpg)
ማኅሌተ ጽጌ ወደ ፊንላንድኛ ቋንቋ ተተርጉሞ ተመረቀ
October 04, 2023
![ሀገረ ስብከቱ የ2015 በጀት ዓመት አፈጻጸም ጠቅላላ ጉባኤውን አጠናቀቀ](http://www.teklehaymanot.fi/wp-content/uploads/2023/09/photo_2023-09-03_22-06-33-420x330.jpg)
ሀገረ ስብከቱ የ2015 በጀት ዓመት አፈጻጸም ጠቅላላ ጉባኤውን አጠናቀቀ
September 03, 2023
![በፊንላንድ ሀገር የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት አዲስ ሕንጻ ቤተክርስቲያን ቡራኬ ተከናወነ !](http://www.teklehaymanot.fi/wp-content/uploads/2023/09/DSC_5323-scaled.jpg)
በፊንላንድ ሀገር የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት አዲስ ሕንጻ ቤተክርስቲያን ቡራኬ ተከናወነ !
September 03, 2023