የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን የልደታቸው ንግሥ በዓል የፊታችን ቅዳሜ ይከበራል

by ግንኙነት ክፍል
+ + +
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
“አእምሩ ከመ ተሰብሐ እግዚአብሔር በጻድቁ” .መዝ. 4,3
“እግዚአብሔር በጻድቁ እንደተመሰገነ እወቁ ” መዝ .4፣ 3
የተከበራችሁ ምእመናንና ምእመናት!
እግዚአብሔር ቢፈቅድ የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን የልደታቸው ንግሥ በዓል የፊታችን ቅዳሜ ታኅሣሥ ፳፫ (Sat Jan 2) በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት ይከበራል ። በዕለቱም የሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አባታችን አቡነ እንጦንስ፣ እንዲሁም ከተለያዩ ሀገራት የሚመጡ የአድባራት አስተዳዳሪዎች ካህናት እና ዲያቆናት ይገኛሉ።ሥርዓተ ዋዜማው ከምሽት ፭ (23:00) ሰዓት ጀምሮ ይከናወናል። የሌሊቱም ሥርዓተ ማኃሌት ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ምእመናን እና ምእመናት በሚገኙበት ተቁሞ ይታደራል። ሥርዓተ ቅዳሴው በሊቀ ጳጳሱ እየተመራ በአባቶች ይከናወንና በመጨረሻም በሊቀ ጳጳሱ ምዕዳን እና ጸሎት የበዓለ ንግሡ ፍጻሜ ይሆናል።
ስለዚህ እርስዎም በእነዚህ ዕለታት በቦታው በመገኘትና ላልሰሙት በማሰማት የበረከቱ ተካፋይ እንዲሆኑ ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች። በዓሉ የሚከበርበት ቦታ እና ሰዓት እንደሚከተለዉ ነዉ።
ንግሥ በዓል
ቀን ፦ ዓርብ ታኅሣሥ ፳፪ – ቅዳሜ ፳፫ ቀን ፳፻፰ (Fri Jan 1 – Sat Jan 2 2016)
ሰዓት፦ ከሌሊቱ 5.00 – ቀኑ 6.30 ሰዓት (23.00 fri – 12.30 Sat )
ቦታ፦ Kristuksen taivaaseenastumisen kirkko (Läntinen Valkoisenlähteentie 48)
ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ
ቀን ፦ እሑድ ታኅሣሥ ፳፬ ቀን ፳፻፰ (Sat Jan 3 2016)
ሰዓት፦ ሰዓት 9:30 – 19:20 (15:30 -19:20 )
ቦታ፦ Opastinsilta 6A, Helsinki
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን!
በኢትዮዽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ በሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት
የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን
ሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት
ፊንላንድ
Recommended Posts

ሀገረ ስብከቱ የ2015 በጀት ዓመት አፈጻጸም ጠቅላላ ጉባኤውን አጠናቀቀ
September 03, 2023

በፊንላንድ ሀገር የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት አዲስ ሕንጻ ቤተክርስቲያን ቡራኬ ተከናወነ !
September 03, 2023

Archbishop Consecrates New Church Building in Helsinki, Finland
September 03, 2023