Uncategorized


28
Apr 2016
የፀሎተ ሐሙስ በዓል በቤተክርስቲያናችን ተከብሮ ዋለ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በየዓመቱ የሚከናወነው የፀሎተ ሐሙስ የእግር አጠባ እና የጸሎተ ቅዳሴት ሥነ ሥርዓት ዛሬ በቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ተከብሮ ውሏል፡፡የደብሩ አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ቀሲስ ለማ በሱፍቃድም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጸሎተ ሐሙስ የደቀ መዛሙርቱን እግር በማጠብ ትህትናን ለደቀመዛሙርቱ ሐዋርያት ያስተማረበት ቀን መሆኑንና እንዲሁም በማግስቱ ዐርብ ስለ ሰዎች ሲል ስለሚቆረሰው ሥጋውና ስለሚፈሰው ደሙ ትምህርት ሰጥተዋል። በመቀጠልም አባታችን የምእመናንን እግር በማጠብ የሕፅበተ እግር ሥርዓትን አከናውነዋል፡፡ አምላካችን እራሱን ዝቅ አድርጎ ያስተማረንን ትህትና እኛ ልንተገብረው ይገባል ብለዋል፡፡ በማያያዝም ነገ ዕለተ ዐርብ የስቅለት በዓል ቀኑን ሙሉ እንደሚከናውን ተገልጿል። ለብርሃነ ትንሣኤው ያድርሰን፡፡  ...

Read More


24
Apr 2016
ቤተ ክርስቲያናች በዛሬው ዕለት አዲስ ድረ ገጽ  አስመረቀች

የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክርለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በዛሬው ዕለት አዲስ ድረ ገጽ  አስመረቀች። በድረ ገጽ ስም www.teklehaymanot.fi በመባል የተሰየመውን ድረ ገጽ መርቀ የከፈቱት የደብሩ አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ቀሲስ ለማ በሱፍቃድ ሲሆኑ የተሠራው ሥራ እጅግ ዘመናዊና ሁሉን ያካተተ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ለምረቃ የበቃው ድረ ገጽ የተሰራው በቤተ ክርስቲያኗ መረጃና ግንኙነት ክፍል ሲሆን እስካሁን የአራት ወር ጊዜ እንደፈጀ ታውቋል። በአሁን ሰዓት ገጹ ላይም የዜና እና መርሐ ግብር፣ የህብር ሚዲያ፣ የህጻናት፣ ትምህርተ ሃይማኖት፣ ስርዓተ ቤተክርስቲያን እና ሌሎች አምዶች አሉት። በምረቃው ላይ ስለ ድረ ገጽ ትንታኔ የሰጠው የመረጃና ግንኙነት ክፍል አገልጋይ ወንድማችን ካቢናድ ተሻገር እንደተናገረ ይህ......

Read More


22
Apr 2016
በሄልሲንኪ ከተማ አውደ ርዕይ ሊካሄድ ነው

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን “የእናት ቤተ ክርስቲያናችንን አደራ እንጠብቅ አንድነታችንንም አንተው” በሚል መሪ ቃል ልዩ የአውደ ርዕይ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሚያካሄድ አስታወቀ። ግንቦት 12 2008 ዓም በሄልሲንኪ ከተማ ይካሄዳል የተባለው መርሐ ግብር አላማው  የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ዕውቅና እንዲኖረው ማድረግ። ወደፊት ስለ ተረካቢ ህፃናትና ከፊንላንድ መንግስትና ለሚመለከታቸው ግንዛቤ መፍጠር በፊንላንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አመሰራረት ታሪክና ዛሬ ያለንበትን ደረጃ ማስተዋወቅ ናቸው። በዝግጅቱ ላይ ከተለያዩ ቤተ እምነቶች ከመንግስትና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች እንግዶች ይጋበዛሉ።አውደ ርዕዩ ከቤተ ክርስቲያኗ 5ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ጋር በጋራ ይከበራል።...

Read More