Blog1 Full Width

26
Aug 2016
አባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት በዓለ እረፍት የዋዜማ በዓል በድምቀት ተከበረ!

በፊላንድ ሄልሲንኪ አሉንኩላን ቤተክርስቲያን የአባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት በዓለ እረፍታቸውን አስመልክቶ የዋዜማ ጉባኤ የደብሩ አስተዳዳሪ ቀሲስ ለማ በሱፍቃድ ፤ ተጋባዥ እንግዶች መምህር ቀሲስ መንግስቱ ጎበዜ(ከስዊድን) ሊቀ መዘምራን ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ(ከኢትዮጵያ) መምህር ፍቃዱ ሣህሌ(ከኢትዮጵያ) ፣ የሰንበት ት/ቤቱ መዘምህራን እና ምዕመናን በተገኙበት በታላቅ መንፈሳዊ ስነ-ስርዓት ተከብሯል፡፡ ሕጻናትም በፕሮግራሙ ላይ ዝማሬን አቅርበዋል። በነገውም ዕለት ከቀኑ 12:00 ሰዓት እስከ 18:00 ሰዓት እንዲሁም ከምሽቱ 22:00 ሰዓት ጀምሮ በተለያዩ የአዳር መንፈሳዊ አገልግሎቶች በሶፊያ የባህል አዳራሽ እንደሚቀጥልም ተገልጾዋል። በዋዜማ ሌሊቱን በማህሌት በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን በጋራ በመሆን መንፈሳዊ አገልግሎት ይቀጥላል።...

Read More


18
Aug 2016
በቫሳ ለመጀመሪያ ጊዜ የቅዳሴና የሥርዐተ ጥምቀት አገልግሎት ተሰጠ

በቫሳና አካባቢው ለሚኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች እሑድ ነሐሴ 8 2008 ዓ.ም. ከሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ወደ ስፍራው በተጓዙ አገልጋዮች አማካኝነት ለመጀመሪያ ጊዜ የቅዳሴና የሥርዓተ ጥምቀት አገልግሎት ተከናውኗል፡፡ በዕለቱ በተካሄደው  መንፈሳዊ አገልግሎት በአካባቢው የሚገኙ የእምነቱ ተከታዮች የተሳተፉ ሲሆን ለሰባት ሕጻናትም  ሥርዓተ ጥምቀት ተፈፅሟል፡፡ ቫሳ ውስጥ መንፈሳዊ አገልግሎት በመደበኛ የሰንበት ጉባኤ አማካኘነት ላለፉት አራት ዓመታት ይሰጥ እንደነበርና፣ የቅዳሴ አገልግሎት ለማግኘት ግን ሕዝበ ክርስቲያኑ ወደ ሄልሲንኪ በመጓዝ  ወይም በሁለት ወር አንድ ጊዜ  በግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በሚዘጋጅ መንፈሳዊ አገልግሎት ይሳተፍ እንደነበር በአገልግሎቱ ላይ የተገኙ ምእመን ገልጸዋል፡፡ በአግልግሎቱ ላይ የተሳተፉ የአካባቢው ነዋሪዎች......

Read More


05
Aug 2016
ጾመ ፍልሰታ

ጾመ ፍልሰታ ፍልሰታ የሚለውን ቃል ትርጉም ስናነሣ ፈለሰ ከሚለው የግዕዝ ግሥ የወጣ /የተገኘ/ ሲሆን በጥሬ ትርጉሙ ከምድር ከመቃብር መለየት፣ ማረግ፤ ወደ ላይ መውጣት የሚለውን ትርጉም ያመለክታል፡፡ በዚህ መሠረት ጾመ ፍልሰታ በአጠቃላይ የእመቤታችን ድንግል ማርያም የሥጋዋን ከመቃብር መለየትና ወደ ገነት ማረጉን የሚያመለክት ሲሆን ቅድስት ቤተክርስቲያን ምዕመናን እንዲጾሙት ከምታዘው ሰባቱ አጽዋማት አንዱና ለዓመቱ ደግሞ የመጨረሻው ጾም ነው፡፡  ይህ ጾመ ፍልሰታ በሌላ አጠራር ጾመ ማርያምም በመባል ይታወቃል፡፡ በዚህ ወቅት በብዛት የሚወሳው /የሚነገረው/ ቃለ እግዚአብሔር በአብዛኛው ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጋር የተያያዘ በመሆኑና የእርስዋ የሥጋዋ ፍልሰት መታሰቢያ በመሆኑ ጾመ ማርያም ተባለ፡፡ ነገር ከስሩ ውኃ ከጥሩ እንዲሉ አበው ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ይህንን የእመቤታችንን ጾም ለምን እንደምታከብር ለመዘርዘር እንወዳለን፡፡ እናታችን ቅድስት ድንግል......

Read More


24
Jul 2016
መወቀር

ክርስትና ሰዉነት ለክርስቶስ ማደሪያ መቅደስነት የተሠራበት የድኅነት መንገድ ነው፡፡ሰው በነፍሱ ወይም ከትንሣኤ በኋላ ባለው ሕይወቱ ብቻ ሳይሆን በዚህ ምድር በሚኖርበት ጊዜም ሰዉነቱ የክርስቶስ ማደሪያ መቅደስ፣ኅሊናዉ ቃሉ የተቀረጸበት ጽላት፣ ልቡናዉም የበጎ ነገር ሁሉ ማደሪያ ታቦት እንዲሆን የተዘጋጀ ነዉ፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳዉሎስ‹‹ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን?… ወይስ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ›› /1ኛ ቆሮ 6፤ 13- 19/ ሲል እንደገለጸልን ሰዉነታችን ለእኛ ፍላጎት ማከማቻነት የተዘጋጀ ቁምሳጥን ሳይሆን የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለመፈጸም የተሰጠን ቅዱስ ንዋይ ነው፡፡ ሐዋርያዉ......

Read More


22
May 2016
በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ደብር የአንድ ቀን ዐውደ ርእይ ተካሄደ

በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ደብር ግንቦት 13/2008 ዓ.ም (May 21 2016) “የእናት ቤተ ክርስቲያናችንን አደራ እንጠብቅ አንድነታችንንም አንተው” በሚል መሪ ቃል ልዩ የአንድ ቀን ዐውደ ርእይ ተካሄደ። ዐውደ ርእዩን መርቀው የከፈቱት የፊኒሽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የተለያዩ ባህል ተጠሪ ቄስ ቴሙ ቶኦይቪነን ፣ ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ አንተነህ ጉደታ በኦስሎ ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም አስተዳዳሪ ፣ የደብሩ አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ለማ በሱፍቃድ ነበሩ ። እንዲሁም ቄስ ሚካኤል ሰንድቪስት ከቲኩሪላ ፊኒሽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን፣ ሚስተር ቬሪኮቨ ሌፍ የሄልሲንኪ ከተማ አስተዳደር የአስተዳደር ክፍል የበላይ ሃላፊ፣ አቶ ኤልያስ ሳቦሬ በፊንላንድ የኢትዮጲያ ኮንስላር በክብር እንግድነተ ተገኝተዋል ።......

Read More


12
May 2016
የጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖትን በዓለ ፍልሠት ከአንድ ቀን  ዐውደ ርእይ ጋር ለማክበር ዝግጅት መጨረሱን አስታወቀ

በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ደብር ግንቦት 13/2008 ዓ.ም(May 21 2016) የጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖትን በዓለ ፍልሠት እንደሚከበር የደብሩ ጽ/ቤት አስታወቀ። በዓሉ በደብሩ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሚከበር የተገለጸ ሲሆን በዕለቱ “የእናት ቤተ ክርስቲያናችንን አደራ እንጠብቅ አንድነታችንንም አንተው” በሚል መሪ ቃል ልዩ የአንድ ቀን አውደ ርዕይ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሚያካሄድ የደብሩ አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ለማ በሱፍቃድ ገልጸዋል። አውደ ርዕዩም በአራት ትዕይንት የተከፈለ ሲሆን በተለያዩ መንፈሳዊ መርሐ ግብሮች በደመቀ ሁኔታ እንደሚታጀብ ተገልጾል። በፊንላንድ እና በአጎራባች ሀገሮች አድባራት የምትገኙ ምእመናን የበዓሉ በረከት ተሳታፊ እንድትሆኑና በዕለቱም ዐውደ ርእዩን እንድትጉበኙ የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት በጻድቁ ስም ጥሪውን ያስተላልፋል። ወስብሐት......

Read More


08
May 2016
ዳግም ትንሣኤ (ለሕፃናት)

ጌታችን በተነሣበት ዕለት የክርስቶስ ደቀመዛሙርት ተሰብስበው ሳለ ጌታችን በመካከላቸው ቆመና “ሰላም ለእናንተ ይሁን “አላቸው፡፡ የነበሩበት ቤት በሩም መስኮቱም ተቆልፎ ስለነበር ደቀ መዛሙርቱም በጣም ደነገጡ፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም “አትፍሩ እኔ አምላካችሁ ነኝ” ብሎ የተወጋ ጎኑን እና የተቸነከሩ እጆቹን አሳያቸው፡፡ እነርሱም ጌታ ከሞት መነሣቱን አመኑ፡፡ ደቀመዛሙርቱንም(ተማሪዎቹንም) ሕዝቡን እንዲያስተምሩ ላካቸው፡፡ በዚህ ዕለት ከ12ቱ ደቀመዛሙርት አንዱ የሆነው ቶማስ ከእነርሱ ጋር አልነበረም፡፡ ደቀመዛሙርቱ የጌታን መነሣት እና እነርሱም እነዳዩት ነገሩት፡፡ እርሱ ግን በዓይኔ ካላየሁ አላምንም አለ፡፡ ከስምነት ቀን በኃላ እንደገና ቶማስ አብሯቸው ሳለ በሩ እንደተዘጋ ጌታችን መጣ፣ በመካከላቸውም ቆሞ “ሰላም ለእናንተ ይሁን” አላቸው፡፡ ቶማስ ትንሣኤውን እነደተጠራጠረ ስላወቀ......

Read More


05
May 2016
የሄልሲን ደብረ አሚን አቡነ የተክለሃይማኖት ደብር በፊላንድ መንግስት እውቅና አገኘ!

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ደብር በፊላንድ መንግስት በቤተክርስቲያን ደረጃ ተመዝግቦ እውቅና መሰጠቱን የደብሩ አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ቀሲስ ለማ በሱፍቃድ አስታወቁ። የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ደብር በማኅበር ደረጃ ከ20 አመታት በላይ ማስቆጥሩ ይታወሳል፤ ይሁንና ላለፉት 5 ዓመት በቤተክርስቲያን ደረጃ ተመዝግቦ በፊንላንድ መንግሥት ዘንድ እውቅና ለማግኘት ከፍተኛ ጥረቶች መደረጋቸውን ተገልፇል። እንደ ደብሩ አስተዳዳሪ ቀሲስ ለማ ገለፃ የተደረጉት ጥረቶች በመጨረሻ ተሳክተው በፊንላንድ ሀገር የመጀመሪያው በሀገሪቱ መንግስት ዘንድ እውቅና የተሰጠው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ በሰሜን ምዕራብ አውሮፓ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን ተብሎ መመዝገቡን ተናገረዋል።......

Read More


02
May 2016
ከትንሣኤ እሁድ በኋላ ያሉ ዕለታት ስያሜ

ከትንሣኤ እሁድ በኋላ ያሉ ዕለታት ስያሜ ✞ ሰኞ- ማዕዶት ይባላል-ማዕዶት ማለት መሻገር, ማለፍ ማለት ነው. በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን , ከሞት ወደ ሕይወት, ከሲኦል ወደ ገነት, ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን. ✞ ማክሰኞ- ቶማስ ይባላል-በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ; ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል. ዮሐ. 20 27-29 ✞ ረቡዕ- አልአዛር ይባላል-በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን . ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ;. የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን ✞ ሐሙስ- አዳም ሐሙስ ይባላል-ዕለት ለአዳም የተሰጠው በዚህ......

Read More