Blog1 Full Width

23
Nov 2017
የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል በድምቀት ተከበረ

በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ዘንድ በየዓመቱ ሕዳር 12 ቀን የሚከበረው የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል ከትላንት በስትያ ከሄልሲንኪ ከተማ ተጉዘው በቦታው በተገኙ ኢትዮጵያውናን እና ኤርትራውናን ሕዳር 9 ቀን 2010 ዓ.ም በፊላንድ በድምቀት  ተክብሯል። ከፊላንድ ዋና ከተማ ሄልሲንኪ 150 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው በቱርኩ ከተማ በሰማዕቱ በቅዱስ አሌክሳንደር የፊላንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ከማላዳው  ጀምሮ በቅዳሴ  የተጀመረው የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል ቀኑን ሙሉ የተለያዩ መንፈሳዊ መዝሙሮች እና ትምህርቶች ቀርበውበታል ። በፊላንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ቀሲስ ለማ በሱፍቃድ የወንጌል ትምህርት ሰጥተዋል።የደብረ አሚን አቡነ......

Read More


29
Sep 2017
የመስቀል ደመራ በዓል ለሁለተኛ ጊዜ በሄልሲንኪ ተከበረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በፊንላንድ ሄልሲንኪደብረ አሚን አቡነተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በሄልሲንኪ ከተማ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን አደባባይ የመስቀል ደመራ በዓል ለሁለተኛ ጊዜ ተከበረ። ከባለፈው ዓመት በተለየ መልኩ የደመራ አዘጋጅ ኮሚቴ ተመርጦ ከፍተኛ ዝግጅት ተደርጎ መስከረም 16 ቀን 2010 ዓ.ም. ከ 17፡30 – 20፡30 በተካሄደው የደመራ ሥነ ሥርዓት ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ በፊንላንድ የሚገኙ የኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ምእመናን እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የልዩ ልዩ ቤተ እምነት መሪዎች ፡ የመንግሥት እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ሓላፊዎችና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በበዓሉ ተገኝተዋል፡፡ በደብሩ ካህናትና ዲያቆናት መሪነት ዕለቱን የሚያዘክር ስብሐተ እግዚአብሔር ከደረሰ  በኋላም በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በዓሉን የሚመለከት ወረብ ቀርቧል፡፡......

Read More


05
Sep 2017
የጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ዓመታዊ የእረፍት  ክብረ በዓል  በታላቅ ድምቀት ተከበረ ።  

ከነሐሴ 24 ቀን እስከ 28 ፥ 2009 ዓ.ም.  ድረስ በታላቅና በልዩ ድምቀት በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ሲከበር በሰነበተው በዚህ ዓመታዊ ክብረ በዓል ላይ ግብዣ የተደረገላቸው በአውሮፓ ከሚገኙ የአብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎች መካከል በኖርዌይ ስታቫንገ  የደብረ ገነት መድኃኔዓለም ወኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪና በሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት የስካንዴኔቭያን ወረዳ ቤተ ክህነት ዋና ፀሐፊ መጋቤ ምሥጢር አባ ቴዎድሮስ አካሉ፣ በኦስትሪያ ቬና የደብረ ሲና  ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉያት ቆሞስ አባ ዘተክለሃይማኖት፣ በኖርዌ ኦስሎ የማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም አስተዳዳሪ መልአከ ምሕረት ቀሲስ ተስፋ ሚካኤል  እንዲሁም በፊንላንድ የሚገኙ የኢትዮጵያ......

Read More


20
Jun 2017
የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊው በዓል በቱርኩ -ፊላንድ በድምቀት ተከበረ!

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዘንድ  በየዓመቱ ሰኔ 12 ቀን  የሚከበረው   ዓመታዊው የቅዱስ ሚካኤል ክብረ  በዓል በቱርኩ- ፊላንድ  ሰኔ 10/2009 ዓ .ም በደመቀ ሁኔታ  ተከበረ። በዘንድሮ ዓመት  ከሌላው ጊዜ በተለየ መልኩ በርካታ ምእመናን ወደ ቱርኩ ተጉዘው በዓሉን ያከበሩ ሲሆን ፣ ከመቼውም ጊዜ  በበለጠ መልኩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሐዶ  እና የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አቢያተ ክርስቲያናት  ካህናት እና ምእመናን በጋራ በተገኙበት በማኅሌትና  በቅዳሴ ከማለዳው  የተጀመረው ክብረ በዓል ቀኑን ሙሉ ቀጥሎ  ከቅዳሴው ፍፃሜ በኋላም  ትምህርትና  እና ልዩ ልዩ መንፈሳዊ  ዝግጅቶች ቀርበዋል ። በፊላንድ  ሄልሲንኪ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ  ቤተክርስቲያን የደብረ አሚን አቡነ  ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን    አስተዳዳሪ  መጋቤ ብሉይ ቀሲስ......

Read More


13
Jun 2017
የተመራቂ ተማሪዎች ልዩ መርሃግብር ተካሄደ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አውሮጳ ሀገረ ስብከት በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ሰኔ ፬ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም (June 11, 2017) ዓ.ም በቀለም ትምህርታቸው ከተለያዩ የትምህርት ተቋማት ለተመረቁ ተማሪዎች ልዩ መርሃ ግብር ተዘጋጀ። በመርሃ ግብሩ መጀመሪያ በደብሩ የስብከተ ወንጌል ክፍል ተጠሪ በተላለፈው መልእክት በዘንድሮ ዓመት የተጀመረው ይህ የተመራቂዎች መርሃ ግብር ወደፊት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል። በተለያዩ የትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን የሚከታተሉ ተማሪዎች ከቀለም ትምህርት ጎን ለጎን መንፈሳዊውንም ትምህርት በሰንበት ትምህርት ቤት ተመዝግበው ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን ከዛሬ በኋላ ተመራቂዎቹ በእውቀታቸውና በመሳሰለው ሁሉ ቤተ ክርስቲያናቸውን እንዲያገለግሉ ጥሪ ቀርቧል ። መርሃ......

Read More


13
May 2017
የትንሣኤና የእመቤታችን የድንግል ማርያም የልደት በዓል ልዩ መርሐ ግብር በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አውሮጳ ሀገረ ስብከት በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በደብሩ ሰንበት ትምህርት ቤት  የሕፃናትና አዳጊዎች  ንዑስ ክፍል የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሣኤ በዓልና የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ ሚያዝያ 29 ቀን 2009 ዓ.ም. (May 7, 2017) ልዩ የሕፃናት እና የአዳጊ ልጆች መርሐ ግብር ተካሄደ።  በመርሐ ግብሩ መጀመሪያ ላይ ከሕፃናት እና አዳጊዎች ንዑስ ክፍል በተላለፈው መልእክት ሕፃናትና  አዳጊ ልጆች የነገ የቤተ ክርስቲያናችን ተረካቢዎች በመሆናቸው ይልቁንም በውጪው ዓለም ለሚገኙ ሕፃናትና አዳጊዎች  የበልጠ ትኩረት በመስጠት  ሃይማኖታቸውን ፣ ቋንቋቸውን እና በጎ ባህላቸውን እንዲያውቁ እና......

Read More


13
Apr 2017
የሆሣዕና በዓል በደማቅ ሁኔታ ተከበረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ሚያዚያ 1 ቀን 2009 ዓ.ም. የሆሣዕና በዓል በደማቅ ሁኔታ ተከበረ። በዕለቱም በየዓመቱ እንደሚከናወነው ሁሉ ቅዳሴ ሥርዓቱ በተለየ ሁኔታ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ቀኖና መሠረት ከተከናወነ በኋላ በቀሲስ ዶክተር አምሳሉ ተፈራ ስለ ሆሣዕና በዓል አጠር ያለ ትምህርት ተሰጥቷል፡፡ የሆሣዕና በዓል ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ አዕሩግም ሕፃናትም ‹‹ ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ፣ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው ፣ሆሣዕና በአርያም›› እያሉ ጌታችንን በክብር መቀበላቸው የሚታወስበት በዓል መሆኑን፤ ‹ሆሣዕና› የሚለው ቃል ‹ሆሼዕናህ› ከሚለው የዕብራይስጥ ቃል የተወሰደ ሲሆን ፣......

Read More


13
Apr 2017
በሶፊያ ባህል ማዕከል ልዩ ዐውደ ጥናት ተካሄደ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን እና በፊንላንድ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የሶፊያ ባህል ማዕከል ትብብር ቅዳሜ መጋቢት 30 ቀን 2009 ዓ.ም. በሶፊያ የባህል ማዕከል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ገዳማትን እና የቅዱስ ያሬድን ዜማ በሚመለከት ልዩ ዐውደ ጥናት ተካሄደ፡፡ በዐውደ ጥናቱም ላይ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ለማ በሱፈቃድ፣ የአጥቢያው ምእመናን፣ የፊንሽ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አባቶች እና የሀገሪቱ ዜጎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ በመጀመሪያ ገዳማዊ ሕይወት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሚል ርዕስ የገዳማዊ ሕይወት አጀማመር፣ ያበረከተው አስተዋጽዖ እና......

Read More


09
Feb 2017
የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ሁለት የወረዳ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤቶችን አዋቀረ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት የወረዳ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤቶችን አዋቀረ። ሀገረ ስብከቱ የመላው አውሮፓ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ ሙሴ መቀመጫ በሆነችው በጀርመን ሀገረ በምትገኘው የሮሰልስሃይም ከተማ ጥር 19 እና 20 ቀን 2009 ዓ.ም ጉባኤውን አካሂዷል። በጉባኤው ላይ የአህጉረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ፣ በሸንገን ስቴት ውስጥ ባሉ የአውሮፓ ሀገራት ያሉ የሀገረ ስብከቱ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎች እና ተወካዮች የተገኙ ሲሆን በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችንም አሳልፏል። ብፁዕ ሊቀ ጳጳሱ በጉባኤው መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት መልእክት በሀገረ ስብከቱ ውስጥ ስብከተ ወንጌልን ለማስፋፋት እና የቤተ ክርስቲያንን......

Read More


25
Jan 2017
በዓለ ጥምቀት በደማቅ ሁኔታ ተከበረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አውሮጳ ሀገረ ስብከት በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ጥር 13 ቀን የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት ቲኩሪላ በሚገኘው በፊኒሽ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በደማቅ ሁኔታ ተከበረ። በዕለቱ በተያዘው መርሃ ግብር መሠረት ሥርዓተ ቅዳሴው ከተከናወነ በኋላ የባህረ ጥምቀቱ ሥርዓተ ጸሎት ተደርሶ ህዝቡም ጸበል ተረጭቶ የበረከቱ ተካፋይ ሆኗል፡፡በመቀጠልም በደብሩ መዘምራን ዕለቱን የተመለከተ  ያሬዳዊ ዜማ የቀረበ ሲሆን  በመጨረሻም በደብሩ አስተዳዳሪ በመጋቤ ብሉይ ቀሲስ ለማ በሱፈቃድ   ትምህርተ  ወንጌል  እና ጸሎተ ቡራኬ ከተሰጠ በኋላ  የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል።...

Read More