Loading Events
  • This event has passed.

የዐቢይ ጾምን ቅበላ በይቅርታ መንፈስ

በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ።” ኤፌሶን 4፥3

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፣

የተከበራችሁ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት አጥቢያ የምትገኙ የጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ልጆች ሆይ!
በሀገራችን ኢትዮጵያ ላለፉት ሁለት ዓመታት እና ከዚያ በፉት በአጋጠመው ጠርነት ፣ እና በመሳሰሉት ነባራዊ ሁኔታዎች የተነሳ በአንዲት እናት ቤተ ክርስቲያን ልጆች መካከል የሻከረ መንፈስ ይስተዋላል።
በመሆኑም የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በሄልሲንኪ እና አካባቢው ያላችሁ የተዋሕዶ ልጆች የተለያዩ ቅሬታዎች ያላችሁ ሁላችሁም እኛ የአንዲት እናት ቤተ ክርስቲያን ልጆች ነንና የሚሰማችሁን ቅሬታ ሁሉ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከልብ በይቅርታ ፈትተን በአንድ ልብ በአንድ መንፈስ ሆነን መጪውን ዐቢይ ጾም ለመጾም እንድንችል ልዩ መርሐ ግብር ተዘጋጅቷል። እነሆ ሁላችሁም ከታች በተጠቀሰው ዕለት እንድትገኙ በታላቅ አክብሮት እናት ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ለልጆች ታቀርባለች ።

እሑድ የካቲት 12/2015 Feb 19/2023
ሰዓት 13:30 -18:00

የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን
ፊንላንድ

Date

February 18, 2023

Time

13:30 - 18:00

Location

Kotikirkko Adarash
Unioninkatu 39
Helsinki, Finland

Organizer

የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን
Phone
+358 40 684 2226
Email
debreaminoffice@gmail.com
View Organizer Website

Share this Event

REGISTER FOR THIS EVENT