Large Posts

04
Aug 2020
የልጆችና የወላጆች ልዩ መርሐ ግብር ተካሄደ

በሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን የተጋጀው ልዩ የልጆችና የወላጆች መርሐ ግብር ለመጀመሪያ ጊዜ ተካሄደ! በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በስዊድንና ስካንዲናቪያን ሀገሮች ሀገረ ስብከት በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በጽጌ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው ልዩ የልጆችና የወላጆች መርሐ ግብር ቅዳሜ ሐምሌ 25/11/2012 በሰሜናዊ ሄልስንኪ በተለምዶ ሃጋ አካባቢ በሚገኘው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ ተከናውኗል። በአይነቱ ልዩ የሆነው የልጆች እና የወላጆች መርሐ ግብርን በጸሎትና ያስጀመሩት የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ አሚን ቀሲስ ለማ በሱፍቃድ ነበሩ። በመቀጠልም መርሐ ግብሩን ያዘጋጁት በጽጌ......

Read More


26
Apr 2020
ቤተ ክርስቲያኗ ልጆቿ ምእመናን  ያሉበትን ሁኔታ የሚከታተል ኮሚቴ ማዋቀሯ ተገለጠ

በስዊድንና እስካንድናቪያን ሀገሮች ሀገረ ስብከት በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ዓለምን እያስጨነቀ የሚገኘው በኮረና ቫይረስ እየቀጠፈ ያለው ሕዝብ በዝርወት ከሚከኙት መካከል ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያ ተጠቃሾች መሆናቸው የሚታወቅ በመሆኑ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት በሥሯ አገልግሎት የሚያገኙትን በመላዋ ፊንላንድ የሚገኙትን ምእመናንን ጤንነት እና አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ የመረዳዳት በጎ ተግባር የሚያስተባብር ኮሚቴ ማዋቀሯን የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ አሚን ለማ በሱፍቃድ ገለጹ፡፡ ኮሚቴው የአጥቢያው ምእመናን በዚህ ቫይረስ ቢያዙ እንኳን አስፈላጊውን ማኅበራዊ ሥነ ልቡናዊና ተመሳሳይ እገዛዎችን ለማድረግ እንደሚያስተባብር ተጠቁሟል ፡፡ ኮሚቴው ከሄልሲንኪ ውጪ ባሉት ምእመናን ባሉባቸው ከተሞችም የመረዳዳት አገልግሎቱን ተደራሽ የሚያደርግበትን አቅጣጫም ማስቀመጡን ታውቋል፡፡......

Read More


21
Jan 2020
በፊንላንድ ሄልሲንኪ የጥምቀት በዓል  በታላቅ  ድምቀት ተከበረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በየዓመቱ ጥር  11 /አሥራ አንድ የሚከበረው የጌታችን የአምላካችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በሄልሲንኪ ደብረ አሚን ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን  በተለየ  ሃይማኖታዊ ድምቀት ተከብሯል። የጥምቀት በዓል በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባሕል ድርጅት (ዩኔስኮ) መመዝገቡን ተከትሎ  ዘንድሮ  ሥርዓቱን በጠበቀና በደመቀ  መልኩ   ታቦተ ሕጉ በምእመናን ታጅቦ ከበዓሉ ዋዜማ  በሚከበረው የከተራ በዓል ጊዜያዊ ማረፊያው ጉዞ አድርጎል:: ከዋዜማው ጀምሮ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ድምቀት የተጀመረው የጥምቀት በዓሉ ሌሊቱን በካህናቱ አገልግሎት አድሮ ከሌሊቱ 10 /አሥር ሰዓት/ ጀምሮ የቅዳሴ ሥነ ሥርዓቱ ቀጥሏል። የቅዳሴው ሥርዓት ከተፈፀመ በኋላ ባሕረ ጥምቀቱ ተባርኮ ሕዝበ ክርስቲያኑም ጠበል ተረጭቷል። የደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ  ቀሲስ......

Read More


29
Aug 2019
በዓለ እረፍቱ ለአቡነ ተክለሃይማኖት በደማቅ ሥነ ሥርዓት ተከበረ

በስዊድንና እካንድናቪያን ሀገሮች ሀገረ ስብከት በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በዓለ እረፍቱ ለአቡነ ተክለሃይማኖት ነሐሴ 18 እና 19/2011 ዓ.ም በድማቅ ሥነ ሥርዓት ተከበረ። በበዓሉ ላይ የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የተገኙ ሲሆን ሌሎችም ከ አውሮጳ ከተለያዩ አድባራት የተጋበዙ ሊቃውንትም በበዓሉ ተገኝተዋል ። ብፁዕ አቡነ ኤልያስ ከበዓሉ ቀደም ብለው ሄልሲንኪ የገቡ ሲሆን ከፊንላንድ ኦርቶዶክስ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሊዮ ጋር የፊንላንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርትሲያን ለቤተ ክርስቲያናችን እስካሁን ላደረገችውና እያደረገች ላለው ትብብር አመስግነዋል። ወደፊትም ለአስፈላጊው አገልግሎት ሁሉ እንዲተባበሩ ጥሪ ከማቅረባቸው በተጨማሪም የጋራ በሆኑ አገልግሎቶች ተባብሮ መሥራትን በተመለከተ በማንሳት ውይይት አድርገዋል ።......

Read More


17
Jun 2019

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በማኅበረ ቅዱሳን አውሮጳ ማዕከል የፊንላንድ ግንኙነት ጣቢያ አዘጋጅነት ለሁለት ቀናት የቆየው መንፈሳዊ ጉባዔ ባለፈው ሳምንት በሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን ልዩ ጉባኤ ተካሄዷል ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ መምህር መጋቤ ሐዲስ በሙሉ አስፋው መሠረታዊ የሃይማኖት ትምህርትን ጨምረው በንስሐ ሕይወት እና በሥርዓተ ቤተክርስቲያን ዙሪያ ሰፋ ያለ ትምህርት ሰጥተዋል ። ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የትምህርት ቤቶች ማደራጃና መምሪያ የማኅበረቅዱሳን በአዉሮፖ ማዕከል የፊንላንድ ግንኙነት ጣቢያ በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ መንፈሳዊ መዝሙሮች እና ሥነጽሑፍ በደብሩ ሰንበት ትምህርት ቤት ክፍል ቀርቧል ። በርካታ......

Read More


16
May 2019
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ ያተኮረ ልዩ ዐውደ ጥናት  በሄልሲንኪ ተካሄደ!

በፊንላንድ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እና በሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን በጋራ የተዘጋጀው ልዩ ዐውደ ጥናት ባለፈው ቅዳሜ ግንቦት 3 2011 ዓ.ም (May 11 2019) በፊንላንድ ሄልሲንኪ በሚገኘው ሶፊያ የባህል ማዕከል በርካታ ምእመናን እና ታዳሚዎች በተገኙበት ተካሄዷል :: ለሦስተኛ ጊዜ በተዘጋጀው እና ጥንታዊቷን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስመልክቶ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ጥናታዊ ጽሑፎች በአንድ ኢትዮጵያዊ እና በሦስት ፊንላንዳውያን ሙሑራን ቀርቧል ። በኢትዮጵያ የሚገኙ ገዳማትና ገዳማዊ ሕይወት ላይ ያተኮረ ጥናታዊ ጽሑፍ በቀዳሚነት በዲያቆን አረጋ ጌታነህ ቀርቦ ግንዛቤ አስጨብጧል። ለረጅም ዓመታት የፊንላንድ ሉተራን ቤተክርስቲያን አለቃ የነበሩት ኒሎ ሆንካነን በነገረ ማርያም ዙሪያ በተለይ ማኅሌተ ጽጌን በተመለከተ......

Read More


19
Mar 2019
የሀገረ ስብከት ምሥረታ ተከናወነ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን አውሮጳ መንበረ ጵጵስናው ስዊድን ስቶኮሆልም የሆነ ሀገረ ስብከት ተመሠረተ ።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለሁለት አሠርተ ዓመታት ያህል በአስተዳደር ተከፍላ ብትቆይም በሐምሌ 2010 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ውሕደቱ ከተፈጸመ በኋላ በጥቅምቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት አውሮጳን ለዐራት አህጉረ ስብከት እንዲከፈል መወሰኑ ይታወቃል ። በዚህ መሠረት በስዊድንና እስካንድንቢያን ሀገሮች እራሱን ችሎ አንድ ሀገረ ስብከት እንዲሆንና በአንጋፋው ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ እንዲመራ በመወሰን የተነሳ መጋቢት 6 እና 7 /2011 ዓ.ም በመንበረ ጵጵስናው ስቶኮሆልም ደብረ ሰላም መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ ሰብሳቢነት ምሥረታው......

Read More


22
Jan 2019
ከሲኖዶሳዊ አንድነቱ በኋላ የመጀመሪያው የጥምቀት እና የቃና ዘገሊላ በዓል በፊንላንድ ሄልሲንኪ ከተማ በጋራ ተከበረ

ከሲኖዶሳዊ ዕርቅና ሰላም በኋላ የመጀመሪያው በዓለ ጥምቀት በሰሜን አውሮፓ በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ÷ ጥር 11 ቀን 2011 ዓ.ም በጋራ ተከበረ፡፡ የበዓሉ የአከባበር ሥነ ሥርዐት እና ጸሎተ ቅዳሴው በደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያ አስተዳዳሪ ÷ በመልአከ አሚን ቀሲስ ለማ በሱ ፈቃድ እየተመራ ÷ከተለያዩ የፊንላንድ ከተሞች የመጡ ኦርቶዶክሳውያን በተገኙበት በጸሎተ ቅዳሴና በትምህርተ ወንጌል በድምቀት ተከብሯል፡፡ በተዘጋጀው የባሕረ ጥምቀት ሥፍራ ስብሐተ እግዚአብሔር ደርሶ፣በሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ዕለቱን የሚያዘክር ወረብ ቀርቦና ከኢትዮጵያ በመጡት መምህር ÷በዲያቆን ታደሰ ወርቁ በዓሉን የተመለከተ ትምህርት ከተሰጠ በኋላ የበዓሉ ፍጻሜ መሆኑ ተዘግቧል፡፡ ከዚሁ ጋራ......

Read More