Blog


05
Jul 2018

የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤ/ክ በሁለቱ ሲኖዶሶች መሓከል የተጀመረውን እርቀ ሰላም እንደሚደግፍ አስታወቀ፡፡ እርቀ ሰላሙን በሚመለከት በወጣው ባለ አምስት ነጥብ የአቋም መግለጫ ላይ እንደተጠቆመው የሁለቱ ሲኖዶሶች አባቶች እርቀ ሰላሙን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈጽሙ፣ ለእዚህም ሂደት የተቋቋመው አስተባባሪ ኮሚቴ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ደብሩ እንደሚደግፍ ተጠቁሟል፡፡ በተጨማሪም፣ በአጥቢያው እና በውጭ አባቶች አስተዳደር ሥር ያሉ ማኅበረ ምእመናን እንዲሁም ሌሎች ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያን የእርቀ ሰላሙን ሂደት እንዲደግፉ እና ለእርቁ መሳካትም አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ተላልፏል፡፡  ...

Read More


25
May 2018
ሰባተኛ ዓመት ምሥረታና ፍልሰተ ዐፅሙ ለአቡነ ተክለሃይማኖት በዓል በደማቅ ሁኔታ ተከበረ

ሰባተኛ ዓመት ምሥረታና ፍልሰተ ዐፅሙ ለአቡነ ተክለሃይማኖት በዓል በደማቅ ሁኔታ ተከበረ በየዓመቱ በታላቅ ድምቀት የሚከበረው ፍልሰተ ዐፅሙ ለአቡነ ተክለሃይማኖት ዓመታዊ ክብረ በዓል እና የደብሩ ሰባተኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በዘንድሮ ዓመት በተለየ ሁኔታ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ በፊንላንድ  የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን ቅዳሜ ግንቦት 11 2010 ዓ.ም ተከብሮ ዋለ :: በዕለቱ ታቦተ አቡነ ተክለሃይማኖት ወደ ፊንላንድ የመጣበት እና ደብሩ እንደ አጥቢያ ቤተክርስቲያን  የተመሠረተበት ሰባተኛ ዓመት “ ሃይማኖታችንን ለልጆቻችን ዛሬ እናስተምር” በሚል መሪ ቃል በፊንላንድ ሄልሲንኪ የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ ሊቀ ማእምራን ቀሲስ ዮሴፍ ምክትል አስተዳዳሪ መልአከ ሰላም ቀሲስ ......

Read More


13
Feb 2018
ልዩ የሕጻናትና አዳጊዎች መርሐ ግብር ተካሄደ

“ልጆቻችሁንም አስተምሩአቸው፥ በቤትህም ስትቀመጥ፥ በመንገድም ስትሄድ፥ ስትተኛም ስትነሣም አጫውቱአቸው” ዘዳ. ፲፩፥፲፱ የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ መመሪያ ምክንያት በማድረግ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አውሮጳ ሀገረ ስብከት በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤት ክፍል የሕፃናትና አዳጊዎች ንዑስ ክፍል አዘጋጅነት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደትና የጥምቀት በዓልን ምክንያት በማድረግ እሑድ ጥር 20 ቀን 2010 ዓ.ም. (January 28, 2018) ከሰዓት በኋላ ልዩ የሕጻናት እና የአዳጊ ልጆች መርሐ ግብር ተካሄደ።   በመርሐ ግብሩ መጀመሪያ ላይ ከሰንበት ትምህርት ቤት ክፍል በተላለፈው መልእክት ሕፃናትና አዳጊዎች ልጆች የነገ የቤተ ክርስቲያናችን ተረካቢዎች በመሆናቸው ለእነርሱ......

Read More


31
Jan 2018

መልካም ጓደኛ.pdf መልካም ጓደኛ  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን በዚህ በምንኖርበት አለም ይብዛም ይነስም አንድ ወይም ከዚያ በላይ ጓደኛ ይኖረናል። በእርግጥ በዚህ ጽሁፍ ዉስጥ ለመግለጽ የተፈለገዉ የወንድ ወይም የሴትን የተቃራኒ ፆታ የፍቅር ጓደኝነትን ሳይሆን መልካም የልብ ጓደኛ ማለት ምን ማለት ነዉ? የሚለዉን ለማየት ሲሆን ምናልባትም ብዙዎቻችን በተለምዶ እገሌ እኮ የእገሌ የልብ ጓደኛዉ ነዉ፤ እገሊትም ለእገሊት የልብ ጓደኛዋ ናት ስንልም እንሰማለን። በአንጻሩ ደግሞ አንዳንድ ሰዎች እገሌ ወይም እገሊት እኮ ጓደኛ አይወጣለትም ወይም አይወጣላትም እንዲያዉ ምክንያቱ ምን ይሆን? በማለት አስተያየት እንሰጣለን። ይሁን እንጅ የልብ ጓደኛ ብለን ስንናገር መለኪያችን ከምን አንጻር እንደሆነ......

Read More


16
Jan 2018
የ2018 ጠቅላላ መንፈሳዊ ጉባኤ ተካሄደ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰሜን ምዕራብ አውሮፖ ሀገረ ስብከት በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን የአጥቢያው ምእመናን በተገኙበት እሑድ ጥር 6 2010ዓ.ም. ወይም Jan 14.2018 በፑኪንማኪ የመሰባሰቢያ አዳራሽ እ.ኤ.አ. የ2018 ጠቅላላ መንፈሳዊ ጉባዔ ተካሄደ፡፡ በጉባኤው መጀመሪያ ላይ የ2017 የክፍሎች የዕቅድ አፈጻጸም እና፣  የሒሳብ ሪፖርት እንዲሁም  የኦዲት ምርመራ ሪፖርቶች ለጉባኤው ቀርበዋል፡፡  ሪፖርቶቹ ከቀረቡ በኋላ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎች እና አስተያየቶች የተሰጡ ሲሆን ለቀረቡ ጥያቄዎችም ከክፍል ተወካዮች እና ከደብሩ አስተዳዳሪ ምላሽ ተሰጥቶ ጉባኤው ሪፖርቶቹን አጽድቋል፡፡ በመቀጠልም እ.ኤ.አ. የ2018 በጀት ዓመት የክፍሎች ዕቅድ ለጉባኤው የቀረበ ሲሆን የቀረበውን ዕቅድ ተከትሎም ከተሳታፊዎች አስተያየት እና ማሳሰቢያ የተሰጠ ሲሆን በተለይ......

Read More


01
Jan 2018
የአቡነ ተክለሃይማኖት የልደት በዓል በታላቅ ድምቀት ተከበረ

በየዓመቱ ታኅሣሥ 24 ቀን የሚከበረው የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖትን በዓለ ልደት ታኅሣሥ 21 ቀን 2010ዓ.ም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን በትላቅ ድምቀት ተከብሮ ውሏል፡፡ ከኢትዮጵያ በመጡ መምህር ዲ.ዶ.ር ቴዎድሮስ በለጠ ከዋዜማው ምሽት ጀምሮ ሥርዓተ ማኅሌቱ እስኪጀመር ድረስ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን፣ የስካንድኖብያ ቤተክህነት ሊቀ ካህናትና በዴንማርክ የኮፐን ሀገን ደብረ ምሕረት አማኑኤል እና ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም አቢያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪ ቆሞስ አባ ዘሚካኤል ፣ በፊንላንድ ሄልሲንኪ የደብረ ሰላም መድኀኔዓለም የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ሊቀ ምእምራን ቀሲስ ዮሴፍ ፣ ካህናትና ዲያቆናት፣ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን፣ ሕጻናት ፣ ከሄልሲንኪና እና......

Read More


27
Dec 2017
ስለ አቤልና ቃየን (ለሕፃናት)

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!! የተዋሕዶ ፍሬዎች፣ የሃገር ተስፋዎች እንደምን ሰነበታችኁ ልጆች? “እግዚአብሔር ይመስገን ደኅና ነን” አላችችኁ? መልካም፡፡ ትምህርት እንዴት ነው? እየጐበዛችኁ ነው አይደል? ጠንከር ብላችኁ በማጥናት ከአምናው የተሻለ ውጤት ለማምጣት እንደተዘጋጃችኁ ተስፋ አደርጋለኹ፤ በርቱ እሺ? ዛሬ አቤል እና ቃየን ስለሚባሉ ኹለት ወንድማማቾች ታሪክ ነው ይዤላችኁ የመጣኹት፡፡ ለመስማት ዝግጁ ናችኁ አይደል? በጣም ጥሩ !!! አዳምና ሔዋን በገነት ይኖሩ ነበር፡፡ ሲበድሉ ግን እግዚአብሔር ከገነት አስወጣቸው፡፡ ደብር ቅዱስ ወደ ተባለ ቦታም ተሰደዱ፡፡ ከዚኽ ቦታ ኾነውም የገነት ሽታ እየሸተታቸው ይኖሩ ነበር፡፡ ወደ ገነት ግን መቅረብ አልተቻላቸውም፡፡ ሦስት ዓመት ሙሉም በጣም ያለቅሱና ያዝኑ......

Read More


26
Dec 2017
ስለ እመቤታችን ልደት (ለሕፃናትና ዠማሪዎች)

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!! ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት ሰነበታችኁ? እግዚአብሔር ይመስገን ደኅና ነን አላችኁ? አሜን፡፡ እኔም በጣም ደኅና ነኝ እግዚአብሔር ይመስገን፡፡ ልጆች! ባለፈው ጊዜ ስለምን እንደተማማርን ታስታውሳላችኁ? አቤል እና ቃየን ስለሚባሉ ኹለት ወንድማማቾች አይደል? ጐበዞች! ትክክል ናችኁ፡፡ ዛሬ ደግሞ ኹላችንም ስለምንወዳት ስለ እናታችን ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት እነግራችኋለኹ፡፡ ለመስማት ዝግጁ ናችኁ አይደል? ጐበዞች፡፡ እግዚአብሔር ዕውቀቱን ይግለጥልን፡፡ አሜን!!! የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አባት ኢያቄም ይባላል፡፡ እናቷ ደግሞ ሐና ትባላለች፡፡ ኢያቄምና ሐና እግዚአብሔርን በጣም የሚወዱትና በሕጉ የሚኖሩ ደጋጐች ነበሩ፡፡ ነገር ግን ሐና መካን ስለነበረች ኹለቱም ወደ ቤተ እግዚአብሔር ዕለት......

Read More


26
Dec 2017
የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በቫሳ ከተማ ተከበረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የቤተክርስቲያን ሰሜን ምዕራብ አውሮፖ ሀገረ ስብከት በፊንላንድ ቫሳ ከተማ የሚኖሩ ምእመናን ባቋቋሙት የቅዱስ ገብርኤል ጽዋዕ ማኅበር አስተባባሪነት ዓመታዊው የቅዱስ ገብርኤል በዓል ባሳለፍነው ቅዳሜ ታኅሣሥ 14 ቀን 2010 ዓ.ም በሥርዓተ ቅዳሴና በጉባኤ ተከብሮ ውሏል። በሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን የሚያገለግሉ ካህናት፤ እንዲሁም ከደብሩ መዘምራን የተወሰኑት ለዚሁ አገልግሎት ከአርብ ጃምሮ በቦታው በመድረስ ቫሳ በሚገኘው የፊንላንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ለምእመናኑ ቅዳሴ ትምህርትና ምክር አገልግሎት ተሰጥቷል። በተለይም ከቅዳሴው በኋላ በተካሄደው ጉባኤ ላይ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ቀሲስ ለማ በሱፈቃድ በዓሉን የተመለከተና ከምእመናን ሕይወት ጋር በማያያዝ ሰፋ......

Read More


24
Nov 2017
ጾመ ነቢያት (የገና ጾም) ኅዳር ፲፭

ጾመ ነቢያት በየዓመቱ ከኅዳር ፲፭ ቀን ጀምሮ እስከ በዓለ ልደት ዋዜማ ድረስ የሚጾም፤ ከሰባቱ አጽዋማት መካከል አንደኛው ጾም ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ዓለምን ለማዳን ሲል የሰውን ሥጋ ስለ መልበሱ፤ ወደ ግብጽ ስለ መሰደዱ፤ በባሕረ ዮርዳኖስ ስለ መጠመቁ፤ በትምህርቱ ብርሃንነት ጨለማውን ዓለም ስለ ማብራቱ፤ ለሰው ልጆች ድኅነት ልዩ ልዩ መከራን ስለ መቀበሉ፤ ስለ መሰቀሉ፣ ስለ ሞቱ፣ ትንሣኤው፣ ዕርገቱና ዳግም ምጽአቱ በየዘመናቱ የተነሡ ቅዱሳን ነቢያት በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝተው ትንቢት ተናግረዋል፤ ትንቢቱ ደርሶ፣ ተፈጽሞ ለመመልከትም ‹‹አንሥእ ኃይለከ ፈኑ እዴከ፤ ኃይልህን አንሣ፤ እጅህን ላክ›› እያሉ በጾም በጸሎት ተወስነው አምላክ ሰው የሚኾንበትን ጊዜ በቀናት፣ በሳምንታት፣ በወራትና በዓመታት እያሰሉ ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡......

Read More