Blog


07
Apr 2016
ጸሎት ክፍል 1

በመ/ር ምሥጢረ ሥላሴ ማናየ ጸሎት ጸለየ፡- ለመነ፣ ጠየቀ አማለደ፣ ማለደ ካለው የግዕዝ ቃል የወጣ ቃል ነው፡፡ ጸሎት ማለት ጠቅለል አድርገን ስንመለከተው ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር እግዚአብሔርን ማመስገን መለመን፣ መጠየቅ፣ መማለድ፣ መማፀን ነው፡፡ “ጸሎት ብሂል ተናግሮ ምስለ እግዚአብሔር፡፡” አባታችን አዳምም ከመላእክት ተምሮ በየሰዓቱ ይጸልይ ያመሰግን ነበር፡፡ ዲያብሎስ በእባብ አድሮ ወደ አዳም በመጣ ጊዜ ጸሎት እያደረገ ስለነበር ዲያብሎስን ድል ነሥቶታል ሔዋንን ግን ሥራ ፈትታ እግሯን ዘርግታ ስለአገኛት ድል ነስቷታል፡፡ ጸሎት ሰማእታት ከነደደ እሳት፣ ከተሳለ ስለት፣ ከአላውያን መኳንንት፣ ከአሕዛብ ነገሥታት ከዲያብሎስ ተንኮል እና ሽንገላ ዲያብሎስ በእነርሱ ላይ ከአጠመደው አሽከላ የዳኑበት ጋሻ ነው፡፡ ኤፌ.6፥10 21 ጸሎት፣ ሰው......

Read More


07
Apr 2016

በዲ/ን ኅብረት የሺጥላ ኪዳን የሚለው ቃል ‹‹ቃል›› ከሚለው ጋር እየተዛረፈ በብሉይ ኪዳን ለ280 ጊዜ ያህል ሲጠቀስ በአዲሰ ኪዳን ደግሞ ከ32 ጊዜ በላይ ተጠቅሷል፡፡ ‹‹ኪዳን›› ቃሉ ‹‹ተካየደ›› ተማማለ፣ ቃል ተገባባ ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ነው፡፡ ‹‹ምሕረት›› የሚለው ቃል ደግሞ ማብራሪያ ሳያሻው ምሥጢሩ ከነዘይቤው ከግእዝ የተወረሰ ነው፡፡ ስለዚህ ኪዳነ ምሕረት ማለት የምሕረት፣ የይቅርታ ውል፣ ስምምነት፣ መሐላ ማለት ነው፡፡ ኪዳን ከተራ ውሎችና ስምምነቶች የበለጠ ጽኑና ቀዋሚ ነው፡፡ ከፍ ያለ ክብደትም አለው፡፡ ‹‹ከመረጥኳቸው ጋር ቃል ኪዳኔን አድርጋለሁ›› ተብሎ በዳዊት መዝሙር እንደተጻፈ እግዚአብሔር ከመረጣቸው ቅዱሳኑ ሁሉ ጋር ቃል ኪዳን አድርጓል፡፡ ወደፊትም ያደርጋል፡፡ (መዝ88.3) ቃል ኪዳኑም የምሕረት ቃል......

Read More


07
Apr 2016
ዳግም ምጽአት

ዳግም ምጽአት ‹‹ደገመ›› እና ‹‹መጽአ›› ከሚሉ ሁለት የግዕዝ ግሦች የተዋቀረ ሐረግ ነው፡፡ የጌታችንንና የአምላካችንን ለሁለተኛ ጊዜ ወደዚህች ዓለም መምጣት ያመለክታል፡፡ የክርስቶስ ዳግም ምጽአት ዳግምነቱ ለልደቱ ነው፡፡ ማለትም ልደቱን ‹‹ቀዳማዊ ምጽአት›› ካልን ዘንድ ለፍርድ መምጣቱን ‹‹ዳግም ምጽአት›› እንላለን፡፡ ‹‹ዳግም›› የሚለውን ቃል አንድ ነገር ያለ ምንም ለውጥ ወይም ልዩነት ሲደገም የምንጠቀምበት ከሆነ ‹‹የተካከለ ዳግም›› እንለዋለን፡፡ ያ ነገር መሠረታዊ ጭብጡን ሳይለቅ ነገር ግን በበርካታ ለውጦች ታጅቦ ከተደገመ ወይም ከቀደመው ጋር ሲነጻጸር ተደገመ የሚያሰኝ ምሥጢራዊ አካሄድ ካለው ‹‹ያልተካከለ ዳግም›› ይባላል፡፡ ፍጹም የሆነ መመሳሰል የሌለው መደገም እንደማለት ነው፡፡ ዳግም ምጽአት፣ ዳግም ልደት፣ ዳግም ትንሣኤ ወዘተ ‹‹ያልተካከለ ዳግም››......

Read More


28
Mar 2016
እናትና አባትህን አክብር (ለሕፃናት)

እንደምን ሰነበታችሁ ልጆች ደህና ናችሁ በዛሬው የመጀመሪያ ጽሑፋችን እናትና አባትን ስለማክበር እንማማራለን ስለዚህ በደንብ ተከታተሉን፡፡ ከነብየ እግዚአብሔር ሙሴ የኦሪት መጻህፍት መካከል አንዱ በሆነው በኦሪት ዘዳግም 5÷16 ላይ እናትና አባትን ስለማክበር እንድህ በማለት ተናተናግሯል ፡- “እግዚአብሔር አምላክህ በሚሰጥህ ምድር ላይ ዕድሜህ እንዲረዝም፣ መልካምም እንዲሆንልህ እናትና አባትህን አክብር፡፡” ዘዳግም 5÷16 ልጆች ከአሥርቱ ትዕዛዛት መካከል አንዱ እናትና አባትህን አክብር የሚለው ነው፡፡ እግዚአብሔር እናትና አባታችንን ካከበርን በምድር ላይ ስንኖር ዕድሜያችን ረዥም እንደሚሆንና፤ በዚህ ዕድሜያችንም መልካም የሆነ ነገር እንደሚያደርግልን ቃል ገብቶልናል፡፡ ለእናትና ለአባታችን ስንታዘዝ እግዚአብሔር በእኛ እንደሚደሰትና እድሜያችንን እንደሚያረዝምልን ሁሉ ካልታዘዝን ደግሞ ያዝንብናል፡፡ እናትና አባቱን የማያከብር፣ ስድብ......

Read More


28
Mar 2016
እኛንም ያድነናል (ለሕፃናት)

እንደምን ሰነበታችሁ ልጆች ? ደህና ናችሁ? እረፍት እንዴት ነው? የዚህ በሁለት ወር ክረምት እረፍታችሁን እንዴት እያሳለፋችሁ ነው? ልጆች ቤተሰባችሁን በመላላክ ሥራ በማገዝ እያገለገላችሁ ነው? በተለይ ደግሞ በቤተክርስቲያን ተገኝታችሁ ትምህርት ቃለ እግዚአብሄርን በመማር በዝማሬ እግዚአብሄርን እያመሰገናችሁ ነው? እንደዚህ ከሆነ በርቱ እሺ እግዚአብሔር የሚወደው እንደዚህ አይነቱን ነው፡፡ እሺ ልጆች ዛሬ ያቀረብንላችሁ ሐምሌ 19 የሚከበረውን ቅዱስ ገብርኤል ስላዳናቸው አንድ እናትና አንድ ልጅ ታሪክ አዘጋጅተንላችኋል በትዕግስት ተከታተሉን እሺ፡፡ የሕፃኑ ስም ቅዱስ ቂርቆስ ሲሆን የእናቱ ስም ደግሞ ቅድስት ኢየሉጣ ትባላለች አባቱ ቆዝሞስ ይባላል፡፡ ሐገሩ ሮም አንጌቤ ነው፡፡ ዲዮቅልጥያኖስ የተባለ ንጉሥ በነገሠበት ጊዜ በ303 ዓ.ም. አብያተ ክርስቲያናትን ማፈራረስ......

Read More


27
Mar 2016
ዓሣ አጥማጁ ስምዖን(ለሕፃናት)

በአንድ ወቅት ምን ሆነ መሰላችሁ ጌታችን በባህር ዳር ቆሞ ሕዝብን ያስተምር ነበር ሕዝቡም ጌታችን የሚያስተምረውን ትምህርት በደንብ ይከታተሉት ነበር፡፡ ጌታችንም ድምጹ ለብዙ ሰዎች እንዲሰማ ወደ ስምዖን ታንኳ ላይ ወጣ፡፡ በታንኳይቱም ውስጥ ተቀምጦ ሕዝቡን አስተማራቸው፡፡ ትምህርቱንም ሲጨርስ ሁሉም ሰው ወደ ቤቱ ሄደ፡፡ ሲማሩ ከነበሩት መካከል አንዱ ስምዖን ነበር፡፡ ቀኑን ሙሉ ሌሊቱን ሁሉ ምንም ዓሣ ስላላጠመደ ተጨንቆ ነበር፡፡ ለምን መሰላችሁ ልጆች የስምዖን ቤተሰቦች ስምዖን የሚያመጣውን ዓሣ ይጠባበቁ ስለነበረ ነው፡፡ ስምዖን ዓሣ ሳይዝ ወደ ቤቱ ከገባ ቤተሰብ ሁሉ ሳይበላ ነው የሚያድረው ማለት ነው፡፡ ነገር ግን ልጆች እግዚአብሔር የስምዖን ቤተ ሰቦች ተርበው እንዲያድሩ አላደረጋቸውም፡፡ ሌላው ደግሞ......

Read More


26
Mar 2016
አትዋሹ (ለሕፃናት)

በድሮ ጊዜ ክርስቲያኖች በአንድነት ይኖሩ ነበር፡፡ በመካከላቸውም የሁሉ ገንዘብ በአንድነት ነበር አንጂ “ይህ የእኔ ገንዘብ ነው” የሚል አልነበረም ከእነርሱም አንድም ችግረኛ አልነበረም፤ ቤትና መሬት ያላቸው ሁሉ እየሸጡ ገንዘቡን ያመጡ ነበር፡፡ አምጥተውም በሐዋርያት እግር ስር ያስቀምጡ ነበር፡፡ ሐዋርያትም ለእያንዳንዱ እንደፍላጎቱ ይሰጡ ነበር፡፡ ሐዋርያት ስሙን ዮሴፍ እያሉ የሚጠሩት በርናባስ የተባለ ሰው ነበር፡፡ የእርሻ መሬትም ነበረው፡፡መሬቱንም ሸጦ ገንዘቡን በሐዋርያት እግር ስር አስቀመጠው ከሐዋርያትም ማኅበር ተቀላቀለ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ልጆች ሐናንያና ሰጲራ የተባሉ ባልና ሚስቶች ነበሩ፡፡ እነዚህ ባልና ሚስቶች መሬታቸውን ሸጡ፡፡ እርስ በርሳቸውም ተማከሩና ከሸጡት ዋጋ ግማሹን ለራሳቸው ወሰዱና የሸጥነው በዚህ ዋጋ ነው ብለው ግማሹን በሐዋርያት......

Read More


01
Jan 2016
የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን የልደታቸው ንግሥ በዓል የፊታችን ቅዳሜ  ይከበራል

+ + + በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። “አእምሩ ከመ ተሰብሐ እግዚአብሔር በጻድቁ” .መዝ. 4,3 “እግዚአብሔር በጻድቁ እንደተመሰገነ እወቁ ” መዝ .4፣ 3 የተከበራችሁ ምእመናንና ምእመናት! እግዚአብሔር ቢፈቅድ የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን የልደታቸው ንግሥ በዓል የፊታችን ቅዳሜ ታኅሣሥ ፳፫ (Sat Jan 2) በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት ይከበራል ። በዕለቱም የሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አባታችን አቡነ እንጦንስ፣ እንዲሁም ከተለያዩ ሀገራት የሚመጡ የአድባራት አስተዳዳሪዎች ካህናት እና ዲያቆናት ይገኛሉ።ሥርዓተ ዋዜማው ከምሽት ፭ (23:00) ሰዓት ጀምሮ ይከናወናል። የሌሊቱም ሥርዓተ ማኃሌት ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ምእመናን እና ምእመናት በሚገኙበት ተቁሞ ይታደራል። ሥርዓተ ቅዳሴው በሊቀ ጳጳሱ......

Read More


14
Nov 2015

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! በፊንላንድ ለምትኖሩ ሕዝበ ክርስቲያኖች በሙሉ፦ በእግዚአብሔር አምላካችን ቸርነት፣ በቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት በጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ጸሎትና ተራዳኢነት፤  የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ብሎም በፊንላንድ ውስጥ የመጀመሪያው ቋሚ ካህን መጋቤ ብሉይ ለማ በሱፍቃድ (ቀሲስ) ለመምጣት በዝግጅት ላይ ናቸው። የእግዚአብሔር ቅዱስ ፍቃዱ ቢሆን አባታችን ቅዳሜ ኅዳር 4 ቀን 2008 ዓ.ም.  (November 14, 2015)  ሄልሲንኪ ይገባሉ።  እግዚአብሔር አምላካችንን እያመሰገንን፤ ለሁላችሁም እንኳን ደስ አለን እንላለን። ለመምህራችንን የእንኳን ደህና መጡ፣በሄልሲንኪ ውስጥና በፊንላድ በተለያዩ ከተሞች ከሚኖሩ ህዝበ ክርስቲያኖች ጋር  የትውውቅ መርሐ ግብር እሁድ ኅዳር 5 ቀን 2008 ዓ.ም. (November 15, 2015) ......

Read More


21
May 2015

Proin eget tortor risus. Curabitur arcu erat, accumsan id imperdiet et, porttitor at sem. Sed porttitor lectus nibh. Vestibulum ante ipsum primis in faucibus orci luctus et ultrices posuere cubilia Curae; Donec velit neque, auctor sit amet aliquam vel, ullamcorper sit amet ligula. Donec rutrum congue leo eget malesuada. Nulla quis lorem ut libero malesuada feugiat. Curabitur non nulla sit amet nisl tempus convallis quis ac lectus. Donec sollicitudin molestie malesuada. Donec rutrum congue leo eget malesuada. Donec sollicitudin molestie malesuada. Nulla quis lorem ut libero malesuada feugiat. Vestibulum ante ipsum primis......

Read More